• Home

ያመለጥንበት የእግዚአብሔር ሕይወት

በተጨነቁ እና መከራ በበዛባቸው ጊዜ ወደ የተሰበሰቡት ወይም ያመለጡበት

 

የሐዋርያት ሥራ 7

11 በግብፅና በከነዓንም አገር ሁሉ ራብና ብዙ ጭንቅ መጣ፥ አባቶቻችንም ምግብን አላገኙም።

12 ያዕቆብም በግብፅ እህል መኖሩን በሰማ ጊዜ በመጀመሪያ አባቶቻችንን ሰደዳቸው፤

13 በሁለተኛውም ዮሴፍ ለወንድሞቹ ታወቀ፥ የዮሴፍም ትውልድ በፈርዖን ዘንድ ተገለጠ።

14 ዮሴፍም አባቱን ያዕቆብንና ሰባ አምስት ነፍስ የነበረውን ቤተ ዘመድ ሁሉ ልኮ አስጠራ።

 

  • የያዕቆብ ቤት ሁሉ የሄዱት ቀድሟቸው ወደ ግብጽ ወደ ገባው ወደ ዮሴፍ ነበር።

 

ኦሪት ዘጸአት 3

12 እርሱም፦ በእውነት እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ እኔም እንደ ላክሁህ ምልክትህ ይህ ነው ሕዝቡን ከግብፅ ባወጣህ ጊዜ በዚህ ተራራ ላይ ለእግዚአብሔር ትገዛላችሁ አለ።

 

  • ፈርዖን እስራኤልን ሁሉ የበኩር ልጆቻቸውን በመግደል ባስጨነቀ ጊዜ የወጡት በምድረ በዳ በነበረው በሙሴ አማካይነት ወደ ምድረ በዳ እግዚአብሔር ወዳለበት ነበር።

 

እግዚአብሔር ያስመለጠን እርሱ ወዳለበት ሕይወት ነው።

 

ወደ ቆላስይስ ሰዎች

1፥13-14 እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን።

 

  • በሚመጣብን በማናቸው ነገር ሁሉ መጠጊያችን የእግዚአብሔር የራሱ ሕይወት ነው።

የተሸነፈ ዓለም

ይህ ዓለም በክርስቶስ የተሸነፈ ነው!

የዮሐንስ ወንጌል 16፥33 በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።

አይኖቻችንን በእግዚአብሔር ላይ እናድርግ

አሁን ያለንበት ጊዜ የሚያስፈራ ቢሆንም፤ እንደ ሁልጊዜውም ዓይኖቻችን በጌታ ላይ ናቸው። ነብዩ ኤርምያስ ይህ ስለገባው የደህንነቱን ተስፋ በእግዚአብሔር ላይ አደርጎት ነበር።

እግዚአብሔር ይግነንባችሁ

ኢየሱስ ኢየሱስ የሚሉ ሰዎች አጋጥመውህ ያውቃሉ? ይህን የሚሉት እርሱ ስለገነነባቸው ነው።

እግዚአብሔር ከስምህ በላይ ነው

ከስምህ እና ከተጠራህበት አቅም በላይ እንድትኖር እግዚአብሔር ጠርቶኃል። ይህም ደግሞ የሚሆነው እግዚአብሔር በክርስቶስ የሰራልንን ስራ በማመን ብቻ ነው።

በክርስቶስ መኖር

በክርስቶስ መጽደቅ



ወደ ገላትያ ሰዎች 2፥17
"ነገር ግን በክርስቶስ ልንጸድቅ የምንፈልግ ስንሆን ራሳችን ደግሞ ኃጢአተኞች ሆነን ከተገኘን፥ እንግዲያስ ክርስቶስ የኃጢአት አገልጋይ ነዋ? አይደለም።"

ክርስቶስ ሰላማችን

ሰላማችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

እረፍት!

More Articles ...

  • 1
  • 2

ይፈልጉ

ይግቡ