ያመለጥንበት የእግዚአብሔር ሕይወት
በተጨነቁ እና መከራ በበዛባቸው ጊዜ ወደ የተሰበሰቡት ወይም ያመለጡበት
የሐዋርያት ሥራ 7
11 በግብፅና በከነዓንም አገር ሁሉ ራብና ብዙ ጭንቅ መጣ፥ አባቶቻችንም ምግብን አላገኙም።
12 ያዕቆብም በግብፅ እህል መኖሩን በሰማ ጊዜ በመጀመሪያ አባቶቻችንን ሰደዳቸው፤
13 በሁለተኛውም ዮሴፍ ለወንድሞቹ ታወቀ፥ የዮሴፍም ትውልድ በፈርዖን ዘንድ ተገለጠ።
14 ዮሴፍም አባቱን ያዕቆብንና ሰባ አምስት ነፍስ የነበረውን ቤተ ዘመድ ሁሉ ልኮ አስጠራ።
- የያዕቆብ ቤት ሁሉ የሄዱት ቀድሟቸው ወደ ግብጽ ወደ ገባው ወደ ዮሴፍ ነበር።
ኦሪት ዘጸአት 3
12 እርሱም፦ በእውነት እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ እኔም እንደ ላክሁህ ምልክትህ ይህ ነው ሕዝቡን ከግብፅ ባወጣህ ጊዜ በዚህ ተራራ ላይ ለእግዚአብሔር ትገዛላችሁ አለ።
- ፈርዖን እስራኤልን ሁሉ የበኩር ልጆቻቸውን በመግደል ባስጨነቀ ጊዜ የወጡት በምድረ በዳ በነበረው በሙሴ አማካይነት ወደ ምድረ በዳ እግዚአብሔር ወዳለበት ነበር።
እግዚአብሔር ያስመለጠን እርሱ ወዳለበት ሕይወት ነው።
ወደ ቆላስይስ ሰዎች
1፥13-14 እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን።
- በሚመጣብን በማናቸው ነገር ሁሉ መጠጊያችን የእግዚአብሔር የራሱ ሕይወት ነው።