Home/መነሻ ገጽ
በጌታ ደስ ይበላችሁ
- Details
- Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
በጌታ ደስ ይበላችሁ ሲል ለምን እንዳለ ማወቁ በጣም ይረዳናል። ሰዎች የሚደሰቱት "ይህ አለን" ብለውና ይህን ያላቸውን ነገር በማሰብና በማሰላሰል ነው። ነቢዩ እንባቆምን በጽሑፉ ስናየው በህይወቱ ሲያስደስቱት የነበሩ ነገሮች ነበሩ። እነዚህ የሚያስደስቱት ነገሮች ከህይወቱ በጎደሉ ጊዜ የሚደሰትበትን ነገር ሲያስብ ጎድሎበት አየ። በዚህ ጊዜ ነው አንድ ከሁሉ በላይ ሊታሰብ የሚገባውን ነገር የተረዳው፤ ይኸውም እግዚአብሔር። ይህ እግዚአብሔር ወገኑ መሆኑን ሲረዳና ሲያስብ ደስታውም ደስታውም በእርሱ መሆኑን ተረዳው። ይህ እግዚአብሔር ለእንባቆም የመድኃኒቱ አምላክ ነበር።
የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው
- Details
- Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
መጽሐፈ ምሳሌ 18፥10 የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው፤ ጻድቅ ወደ እርሱ ሮጦ ከፍ ከፍ ይላል።
የእግዚአብሔር ስም ለሚታመኑት በከፍታ እንደተሰራ የመጠከለያ ግንብ ነው። ጠላት ያለውን ሁሉ ቢወረውር በዚህ ስም የተከለለውን ሊነካው አይችልም። ስሙ የጸና ግምብ ነው።
በከፍታ ስፍራ እንደተቀመጠ ሰው በዚህ ስም የተደገፈ ሁሉ እንደዚሁ በከፍታ ስፍራ ሆኖ ይጠበቃል። የጻድቅም ተስፋው የእግዚአብሔር ስም ነው። ጻድቅ ሁልጊዜ የሚሮጠው ወደዚህ ስም ነው።
የእግዚአብሔር ፍቅር
- Details
- Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
የእግዚአብሔር ፍቅር በመንፈስ ቅዱስ ስለፈሰሰልን ሰዎችን ሁሉ መውደድ ሆኖልናል። ፍቅርን የምንፈጥረው ሳይሆን የምንቀበለው እንደሆነ በዚህ እናያለን። ይህም ፍቅር ደግሞ የእግዚአብሔርን ባህርይ ያሳየናል።
በክርስቶስ ሥራ ማረፍ
- Details
- Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
ክርስቶስ የመጣው ሊያሳርፈን ነው። እኛ ልንፈጽመው ያልቻልነውን የጽድቅን ሥራ እርሱ ፈጽሞልን በእኛ ላይ የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደምስሶታል። ይህም የዕዳ ጽሕፈት ይቃወመን እና ይከሰን የነበረ ትእዛዝ ሲሆን ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀሉ ስራ ከመንገዳችን ላይ አንስቶታል። ስለዚህም ዳግመኛ በዚህ ትእዛዝ ላንያዝ ዘንድ ነጻ ወጥተናል። ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ተሰቅሎ፣ ሞቶ፣ ተቀብሮ ደግሞም ከሙታን ተነስቶ ወደ ነጻነታችን አስገብቶናል። እንኳን በክርስቶስ ኢየሱስ ወደዚህ የእረፍት ነጻነት መጡ። ክብር ለስሙ ይሁን።
ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2፡14 በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤
Page 4 of 5