yegizewkal
ቃልህ ተገኝቶአል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ፥ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ። ትንቢተ ኤርምያስ 15፥16

  • Home/መነሻ ገጽ
  • Gospel Thoughts/የወንጌል አስተምህሮ
    • ነገረ ድነት/Salvation
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
    • Literature/ስነ-ጽሑፍ
    • ከመጽሐፍት ዓለም
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን
    • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Testimony/ምስክርነት
  • ማስታወቂያ/Advertisement
  1. You are here:  
  2. Home
  3. The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የትውልድ አደራ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

 

የትውልድ አደራ

የትውልድ ባለአደራነትን መወጣት

አደራ ለአንድ የተወሰነ ተግባር እና ክዋኔ ወይም ግዴታ ለአንድ ሰው ሃላፊነት ወይም ስልጣን መስጠት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን፣ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት እና በኃላፊነት እንዲወጣ እምነትን መጣል ሲሆን፣ አደራ የአደራን ተግባር በአደራ፣ በመተማመን እና በአደራ የተሰጠው ሰው አቅም ላይ በማመን ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይችላል። 

 

አደራን የመወጣት እና አደራን ከግብ ማድረስ እንዴት ያለ መታደል ነው። በተለይ የትውልድን አደራ ተቀብሎ ትውልድ በመልካም መንገድ የእግዚአብሔርን ሕግ ተከትሎ እንዲሄድ አድርጎ እና በዚህም ፍሬን ማየት እንዴት እጅግ ያስደስታል። 

ትውልድን ከክፋት ነጥሎ ትውልድን በእውነት መንገድ እንዲሄዱ ማድረግ፣ ከእግዚአብሔርም ጋር ማገናኘት እንዴት አይነት ትልቅ ሥራ ነው? በእውነት መንገድ ሄደውም ማየትን የመሠለ ነገር የለም። 

በተለይ በትውልድ ላይ በእውነትና በሐቅ እየለፉ፣ እየታተሩ ያሉ ምን ያህል ለውጤት እንደሚተጉ ሲታዩ የጭንቀታቸውን ልክ በጥቂቱ መገመት የሚቻል ቢሆንም እውነታውን የሚረዳው አይነቱ እና እራሱ ባለቤቱ ነው። 

አለም የራሷን ትውልድ ገዳይ አሰናድታ ባስቀመጠችበት ዘመን ቤተክርስቲያን በመዘናጋት ለገዳይ እድልን መስጠቷ ከመዘናጋቷም የተነሳ አጥፊው እየተጋ ባለበት ዘመን አለመንቃት የነገ ተስፋዎቿ እየተነጠቁባት መሆኑ ለአፍታም ግድ ያላላት ምን ልትሠራ? ሥራዋስ ምን እንደሆነ ጠንቅቃ አለማወቋ ትውልድ ከማህፀን ጀምሮ እየመከነ መሆኑ አለመረዳቷ የነገ የቤተክርስቲያን ተስፋዋ ጭምር እየጠፋ መሆኑን አሳሳቢ ጉዳይ ሆኖአል። “የግብፅም ንጉሥ አንዲቱ ሲፓራ ሁለተኛይቱም ፉሐ የሚባሉትን የዕብራውያንን አዋላጆች እንዲህ ብሎ ተናገረ።” — ዘጸአት 1፥15። “እናንተ የዕብራውያንን ሴቶች ስታዋልዱ፥ ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፥ ወንድ ቢሆን ግደሉት ሴት ብትሆን ግን በሕይወት ትኑር።” — ዘጸአት 1፥16። “የግብፅም ንጉሥ አዋላጆችን ጠርቶ፦ ለምን እንዲህ አደረጋችሁ? ወንዶቹን ሕፃናትንስ ለምን አዳናችሁ? አላቸው።”— ዘጸአት 1፥18። የነቁትም ቢሆን እጅግ ጥቂት መሆናቸውና ሥራውም ሰፊ ከመሆኑ አኳያ አለመጣጣሙ ትውልድን ከጥፋት መመለሱ በበቂ ሁኔታ እየተሠራ አለመሆኑ ትልቁ ማሰያና ማረጋገጫ ነው። “አዋላጆች ግን እግዚአብሔርን ፈሩ፥ የግብፅ ንጉሥም እንዳዘዛቸው አላደረጉም፥ ወንዶቹን ሕፃናትንም አዳኑአቸው።” — ዘጸአት 1፥17። “አዋላጆቹም ፈርዖንን፦ የዕብራውያን ሴቶች እንደ ግብፅ ሴቶች ስላልሆኑ፤ እነርሱ ጠንካሮች ናቸውና አዋላጆች ሳይገቡ ስለሚወልዱ ነው አሉት።” — ዘጸአት 1፥19።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር በነበረበት ዘመን ለትውልድ ያለውን የጠለቀ ፍቅሩን የገለጠበት መንገድ የሁላችን አእምሮ ውስጥ ያለ ነው። ህፃናት የነገ ተስፋዎች መሆናቸውን ከተናገረበት ንግግር አኳያ መረዳት ይቻላል። ብዙውን ጊዜ ትልልቆች በተሠበሰቡበት የትኛውም ስፍራ ህፃናት እንዲደርሱ አሊያም እንዲገኙ ጨርሶ አይፈቀድላቸውም። "ልጅ ያቦካው ለእራት አይበቃም" በሚል ከንቱ ብሂል ህፃናትን እናሳንሳለን፣ እንዲጠጉንም አንሻም፣ አናምናየውም። በእርሪልጅ ባለበት ጥፋት እንደማይጠፋ ይታወቃል፣ አርቆ ማሳደጉ የእኛ ድርሻ ነው፣ ከአይናችንም ባይርቁ መልካም ነው።

ጌታ ኢየሱስና ጴጥሮስ
ዮሐንስ 21:15፣ ለጴጥሮስ የተሰጠው የትውልድ አደራ የሁሉንም የዕድሜ ክልል ያካተተ ሲሆን፣ በተለይ "ቤተክርስቲያኔን በአንተ ላይ እመሰርታለሁ" ማለቱ ምን ያህል ቤተክርስቲያን የትውልድን አይነት ይዛ እንደምትገኝ ማሳያ ነው። ለዚህም ነው ለጴጥሮስ የተሠጠው የትውልድ አደራ ከብዶና በተደጋጋሚ መጠየቁ የጉዳዩ የአደራ ክብደቱን፣ አሳሳቢነትና ኃላፊነትን የሚያሳየው። ስለዚህ በአደራ ባለቤትና ሰጪው ልክ ተረድተን አደራን መወጣት አለብን። ለውጤታማነትና ለፍሬያማነቱም መትጋቱም ጭምር ታሳቢ ማድረጉ መልካም ነው። ቆጥሮ የሰጠን ቆጥሮ ይረከበናል።

መልዕክተኛው_ዮሐንስና_ልጆቹ
የአንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ሶስተኛ መልዕክት ፀሐፊው
ዮሐንስ ከመልዕክቱ እንደምንረዳው ምን ያህል ከስሩ ባሉት ላይ እንደሠራና ተደስቶም  ስለ እነርሱ ከሌሎች የሰማውን ምስክርነት፣ የተመሰከረውን በመጥቀስ መናገሩ የልፋቱን ውጤት ማየቱ እንዳስደሰተው በመልዕክቱ ሲናገር እናየዋለን። የልፋቱን ልክ በዙሪያቸው ባሉት ሰዎች ምስክርነት መሠጠቱ የዘራውን ዘር በሌሎች ዘንድ ተዘርቶ ማየቱ እና ፍሬው ወደ ሌሎች መሻገሩ ምን ያህል ደስታን እንዳጫረበት መመልከት ይቻላል።  “ሽማግሌው በእውነት እኔ ለምወደው ለተወደደው ለጋይዮስ።”— 3ኛ ዮሐንስ 1፥1።

“ወንድሞች መጥተው አንተ በእውነት እንደምትሄድ ስለ እውነትህ ሲመሰክሩ እጅግ ደስ ብሎኛልና።” — 3ኛ ዮሐንስ 1፥3። “ለድሜጥሮስ ሁሉ ይመሰክሩለታል፥ እውነት ራስዋም ትመሰክርለታለች፤ እኛም ደግሞ እንመሰክርለታለን፥ ምስክርነታችንም እውነት እንደ ሆነ ታውቃላችሁ።” — 3ኛ ዮሐንስ 1፥12። “ልጆቼ በእውነት እንዲሄዱ ከመስማት ይልቅ የሚበልጥ ደስታ የለኝም።” — 3ኛ ዮሐንስ 1፥4።

ዛሬስ በዚህ ዘመን ያለን እግዚአብሔርን እና የእግዚአብሔርን ሕዝብ የምናገለግል፣ አደራ የተሰጠን በእርግጥ የቀደሙት አባቶች እንዳደረጉት ዛሬም እንዲሁ እያደረግን ይሆን? የትውልድን አደራ ተሸክመን ያለን ተገቢውን ነገር እያደረግን ይሆን?

“ልጆቼ ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ኃጢአተኛ በማድረጋችሁ ስለ እናንተ የደረሰኝ ወሬ መልካም አይደለምና ይህ አይሆንም።” — 1ኛ ሳሙኤል 2፥24።

 ትናንት ትውድን ሊያጠፋ የሞከረ ፈርኦን በቀጣይ በሄሮድስ የቀጠለው ዛሬም ትውልድን ሊያጠፋ የተዘጋጀ መልኩንም፣ ስሙን፣ አይነቱንም፣ አሰራሩንም ቀይሮ የተዘጋጀ መኖሩን ለቅፅበት መርሳት የለብንም። ይልቁን መልኩን ቀይሮ በመምጣት ትውልድን ለራሱ ሊማርክና ብሎም ሊያጠፋ የቆረጠን የጨለማ ተልዕኮ አስፈፃሚን እኛ በእግዚአብሔር ፊት በምናደርገው የትኛውም ትጋት ተልዕኮውን እንደምናፈርስ መዘንጋት የለብንም።

የቤተክርስቲያን_መሪና_ተተኪ_ትውልድ

 ዛሬ ላይ በዚህን ጊዜ የቤተክርስቲያን ተልዕኮ ሙሉ በሙሉ በይሆንም እጅግ በአብዛኛው የነገ ተስፋ የሆኑት ትውልድ   ላይ እየሰራን አለመሆኑ አልታወቀንም። እየሠሩ ነው የሚባል መከራከሪያ ነጥብ እንኳን ቢነሳ ተልዕኮውና አላማው       ከራስ ጥቅምና ፍላጎት የተነሳ እንጂ የትውልድ አደራነት ተሰምቶት የሚሠራው እጅግ ጥቂት ነው። "የመከሩ ሠራተኞች ጥቂቶች ናቸው" የሚለውን የእግዚአብሔርን ቃል ማሰቡ እጅግ ተገቢ ነው። 

መሪነት አንድም በደጅ አንድም በቢሮ ተቀምጠን ብቻ የምንሠራው ሥራ አይደለም። ለተጠራንበት አላማ ለግቡ መሳካት አውራውን ሥራ መሥራት አለብን። የፈዘዘ፣ የደነዘዘ በምንም አይነት መልኩ ሥራ አይሠራም፣ አጥፊ ትውልድን እንኳን በቅጡ አይመክርም፣ አይገስፅም፣ አይቆጣም፣ ልጆችህ እንዲህ አደረጉ ቢባል እንኳን "እግዚአብሔር የወደደውን ያድርግ" በሚል ሽንፈትና ተስፋ መቁረጥን ያዘለ ከመፍትሔ መሸሻና ማምለጫ ሃሳብን በመሰንዘር ጉዳዩን ወደ ጎን መተው መጨረሻው አያምር አይነት ይሆናል። ትውልድን የሚያረክስና የሚያበላሽ ትውልድ ከመምጣቱ በፊት በእጅ ያለን ትውልድ ከወዲሁ አርቆ ማስተካከሉ መሠረቱን ማስተካከል እንደሆነ ማወቅ ይጠቅመናል። ነገን ዛሬ ላይ እንሥራ። 

ካህኑ ኤሊ እና ልጆቹ

“ዔሊም እጅግ አረጀ፤ ልጆቹም በእስራኤል ሁሉ ላይ ያደረጉትን ሁሉ፥ በመገናኛውም ድንኳን ደጅ ከሚያገለግሉት ሴቶች ጋር እንደ ተኙ ሰማ።” — 1ኛ ሳሙኤል 2፥22። ጥፋተኛን አይተን፣ ስለጥፋተኛ ሰምተን "ጆሮ ዳባ ልበስ"፣ "የዝሆን ጆሮ ይሰጠን" ባንል መልካም ነው። “እርሱም አላቸው፦ ስለ ክፉ ሥራችሁ ከዚህ ሕዝብ ሁሉ ሰምቻለሁና ስለምን እንዲህ ያለ ነገር ታደርጋላችሁ?”— 1ኛ ሳሙኤል 2፥23።
“ልጆቼ ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ኃጢአተኛ በማድረጋችሁ ስለ እናንተ የደረሰኝ ወሬ መልካም አይደለምና ይህ አይሆንም።” — 1ኛ ሳሙኤል 2፥24። እግዚአብሔር ከምናምንቴዎች ጋር እንደማይሠራ ልብ ልንል ይገባል።

ነቢዩ ሳሙኤል እና ልጆቹ

ነብይ ሳሙኤል በዘመኑ ሀገር ምድር ያረፈችበት፣ እግዚአብሔርም ያረፈበት፣ እስራኤል ከጠላቱ ከፍልስጥኤማውያን ያረፈችበት ትልቅ ነብይ የነበረ በሞቱ እንኳን እስራኤል ለቀናት ያለቀሰችለት ትልቅ ነብይ ነበረ። (እንዲህ አይነት መሪ ይስጠን! አሜን!) የነብዩ ሳሙኤል ልጆች ግን እሱ በሄደበት መንገድ ልክ አልሄዱም። በአባታቸው እግር ተተክተው ያገለግላሉ ተብለው የተሾሙና የተቀመጡ አባታቸው በሕይወት ዘመኑ ያልሄደበትን መንገድ በመሄድ እግዚአብሔር በማይፈልግበት መንገድ ሕዝብ እንዲሄድ ከደረጉ፣ የሕዝብንም ልብ ከእግዚአብሔር አሸፈቱ፣ የአህዛብን ስረዓት እንዲመኙ አደረጉ።  “እነሆ፥ አንተ ሸምግለሃል፥ ልጆችህም በመንገድህ አይሄዱም፤ አሁንም እንደ አሕዛብ ሁሉ የሚፈርድልን ንጉሥ አድርግልን አሉት።” — 1ኛ ሳሙኤል 8፥5። “የሚፈርድልንም ንጉሥ ስጠን ባሉት ጊዜ ነገሩ ሳሙኤልን አስከፋው፤ ሳሙኤልም ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።” — 1ኛ ሳሙኤል 8፥6።
       

              በመጨረሻም:-
የመፍትሄ_ሐሳብ፡ 
1. የሚሄድበትን መንገድ መምራት
       1.1. ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ማገናኘት
እጅግ ከማቅረብና ከመቅረብ በቀጠለ ትውልድ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ማቆራኘት፣ እንዲጠብቅና እንዲያሰላስል ማድረግ። “ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ።” — ምሳሌ 3፥1።

ልጅን አግባብ በሆነ መልኩ ከእግዚአብሔር ቃል አኳያ ማስተማር፣ ለነገ እንደሚጠቅመው እና የእግዚአብሔር ቃል ዋስትና እንደሆነ ማሳየት። 

   1.2. ልጅን ማሰልጠን፣ ማስተማር
“ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።” — ምሳሌ 22፥6።

“Train up a child in the way he should go: and when he is old, he will not depart from it.” — Proverbs 22፥6 (KJV)

2.  ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ማገናኘት
ኢያሱና ሰለሞን የተነገራቸው የእግዚአብሔር ቃል ምክር ሲነገራቸው የነገን፣ የወደፊቱን ነገራቸው የሚሳካው በእግዚአብሔር ቃል ላይ በመመርኮዝ ብቻ እንደሆነ አጠንክረው ነገረዋቸዋል።

    2.1. እግዚአብሔር ሙሴ ለኢያሱ የነገረውን ኢያሱን ሲያስታው፦
“ነገር ግን ጽና፥ እጅግ በርታ፤ ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ፥ አድርገውም፤ በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል።” — ኢያሱ 1፥7። 

    2.2. ዳዊት ልጁን ሰለሞንን የመከረው ምክር
“በርታ ሰውም ሁን፤ የምታደርገውንና የምትሄድበትን ሁሉ ታከናውን ዘንድ፥ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈ ሥርዓቱንና ትእዛዛቱን ፍርዱንና ምስክሩንም ትጠብቅ ዘንድ፥ በመንገዱም ትሄድ ዘንድ፥ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።” — 1ኛ ነገሥት 2፥3።

3. በአደራነትና በኃላፊነት መምራት
መፅሐፍ ቅዱሳችን በትውልድ ላይ የአደራነትን ተልዕኮ የተሰጠው ሐዋሪያው ጴጥሮስ ተደጋግሞ የተነገረው ጉዳይ ቢኖር በእያንዳንዱ የዕድሜ ደረጃ ያሉትን ምን እንዲያደርግላቸው እንደሚገባ ጌታችን ኢየሱስ በመንገርና አደራን በመስጠት ነግሮታል። ዛሬም በዚህ ዘመን ላለን ይህንኑ አደራ እንደተቀበልን ማወቅ አለብን። ዮሐንስ 21:15-18 መመልከት ይቻላል።

4. ቤተሰባዊ ምክር መለገስ
ንጉስ ዳዊት ልጁን ሰለሞንን አንድም እንደ ሃገር መሪ፣ አንድም እንደ ወላጅ አባት ምክሩን ከእግዚአብሔር ቃል አኳያ ነግሮታል። አደራውን ተወጣ። “በርታ ሰውም ሁን፤ የምታደርገውንና የምትሄድበትን ሁሉ ታከናውን ዘንድ፥ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈ ሥርዓቱንና ትእዛዛቱን ፍርዱንና ምስክሩንም ትጠብቅ ዘንድ፥ በመንገዱም ትሄድ ዘንድ፥ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።” — 1ኛ ነገሥት 2፥3። “እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጡአቸው።” — ኤፌሶን 6፥4። “እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ።” — ዘዳግም 6፥6። “ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው።” — ዘዳግም 6፥7።

አደራን መወጣት ይሁንልን!
በረከት ሱላሞ ሱጌቦ

የተፅእኖ ሰው

Details
Written by: BEREKET SULAMO SUGEBO
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የተፅእኖ ሰው

እነርሱ በእምነት መንግስታትን ድል ነሡ ጽድቅን አደረጉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ

ዕብራውያን 11፡33

በምድራችን ላይ በየትኛውም ዘመን በታሪክ መዛግብት እና በአፈ ታሪክ እንደሚነገረን፣ ከኖርንባቸው ዘመናት ቀድመው የኖሩ በፍልስፍናቸው አመለካከት ይሁን፣ በÞለቲካ አመለካከታቸውና ፍልስፍናቸው ይሁን፣ በፈጠራ ሥራና ግኝት ልህቀት ይሁን፣ ብቻ በተሰማሩበት በየትኛውም ዘርፍ ተፅዕኖን ፈጥረው ለዓለም የሚጠቅም አዎንታዊ ይሁን፣ የማይጠቅም አሉታዊ ጉዳይ ይሁን ሰርተው አልፈዋል፣ አንቱታንም ተችረው፣ ተሞግሰው ለበጎ ነገር ይሁን ለዕኩይ አንድ አሻራ ጥለው አልፈዋል፡፡

Read more: የተፅእኖ ሰው

ያልተጎሰመ አንደበት

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ


tongue

ያልተጎሰመ አንደበት

“አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ።”— መዝሙር 34፥13። 

በአለም ላይ የተደረጉ የትኛውም አይነት ጦርነቶች በቅድሚያ ውጊያን የጀመሩት በዘመናቸው በነበሩት የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም በአንደበት ነው። ክፉ አንደበት የጠብ ጫሪነትን ሚና በከፍተኛ ደረጃ የምትወጣ የክፉ አለም ተምሳሌት ነች። የጦርነት ክተት ይሁን አዋጅ በነጋሪት ጉሰማ ሲታወጅ አንደበት የጦርነትን መጀመር ፋና ወጊና ፈር ቀዳጅ አንደበት ነው። በአንደበት በትንሽ ምላስ የተጫረ የጦርነት ምላጭ ተኩስ የተጀመረው በዚህ በአንደበት አለም ነው። 

በክርስትናውም አለም እንዲሁ ያልተጎሰመ አንደበት ሥራው ይኸው ሲሆን በተለይ በወንድማማች መካከል ጠብን በመዝራት የሚታወቀው ይኸው ያልተገራው አንደበት ነው። በተለይ በዚህ ባለንበት ዘመን እጅግ ብዙ አገልጋዮች በድብደባና በዱላ ከመሰበር በላይ በአንደበት የተሰበሩት ኅልቁ መሳፍርት ናቸው። 

በብሉይ ኪዳን ዘመን እንኳን ስንመለከት ሙሴ ከላካቸው አስራ ሁለቱ ሰላዮች የአስሩ መረጃ የሕዝበ እስራኤልን ልብ ያቀለጠ መረጃ ነበር። በተለይ ከአፋቸው የሚወጣው ንግግር የሕዝቡ ልብ እስኪቀልጥ ድረስ እና በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ እስኪነሱ ድረስ ያደረሰን ተገቢ ያልሆነን መረጃ ይዘው በመምጣት የህዝብን ልብና ጉዞ አውከዋል። “ከእኔ ጋር የወጡ ወንድሞቼ ግን የሕዝቡን ልብ አቀለጡ፤ እኔ ግን አምላኬን እግዚአብሔርን ፈጽሜ ተከተልሁ።” — ኢያሱ 14፥8። 

የብዙዎች ሕይወትና አገልግሎት እንዲሁም ሩጫቸው የተቃጠለውና የተመታው በአንደበት አለም በተደረገው ጦርነት ነው። በሰውነታችን ላይ ካሉት ብልቶቻችን ወይም የሰውነት ክፍሎቻችን መካከል እጅግ አደገኛው አካል ወይም ብልት አንደበት ነው። አጥንት እስኪሰበር የሚያደርስን ክፋት የተሞላ መርዛማ ነገር ነው። 

“እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል።”— ያዕቆብ 3፥5። 

“አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።”— ያዕቆብ 3፥6።


በተለይ በመፅሐፍ ቅዱሳችን ስለ አንደበት የተነገረው ቃል እጅግ አሉታዊ በሆነ መንገድ የተገለጸው ነው። ስለ አንደበት በዝርዝር በማንነቱና በባህሪው የተገለጠበት መንገድ፦
1. ትንሽ ብልት
2. በታላላቅ ነገር ይመካል
3. እሳት 
4. ዓመፀኛ አለም
5. ሥጋን የሚያሳድፍ
6. ሩጫን የሚያቃጥል
7. በገሃነምም የሚቃጠል እንደሆነ በግልፅ ተቀምጧል። 

በተለይ በነህምያ እና በዕዝራ ዘመን የፈረሰችውን እየሩሳሌምን በሚጠግኑበት ጊዜ በዙሪያቸው የነበሩት ጠላቶቻቸው የመጀመሪያውን ጦርነት የጀመሩት በአንደበት ጦርነት በሚያናንቅና በሚያጥላላ ንግግር ነው። “አሞናዊውም ጦብያ በአጠገቡ ቆሞ፦ በድንጋይ በሚሠሩት ቅጥራቸው ላይ ቀበሮ ቢመጣበት ያፈርሰዋል አለ።” — ነሀምያ 4፥3። አንደበት የዚህን ያህል ውስጥን የሚያበግን ንግግርን አፍልቆ ስሜትን ይነካል። ለዚህ ነው ነህምያ በምላሹ፦ “አምላካችን ሆይ፥ ተንቀናልና ስማ፤ ስድባቸውን በራሳቸው ላይ መልስባቸው በምርኮ አገር ለብዝበዛ አሳልፈህ ስጣቸው።” — ነሀምያ 4፥4። “በደላቸውንም አትክደን፥ ኃጢአታቸውም ከፊትህ አይደምሰስ፤ በሠራተኞች ፊት አስቆጥተውሃልና።” — ነሀምያ 4፥5። 

የአለማውያኑ ንግግር ይህን ያህል ላይጎዳ ይችላል፣ ምክንያቱም የባህሪያቸው ስለሆነ ቦታ ላንሰጠው እንችል ይሆናል። ሆኖም ግን በእኛ በክርስቲያኖች መካከል የሚደረገው የአንደበት ላይ ጦርነቶች በብዙ አኅዛብ መካከል መሳለቂያ እስከመሆን ደርሰናል። በተለይ በመፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ላይ ያለን የሰፋ ልዩነትና የምንሰጣጣቸው ምላሾች በብዙዎች ዘንድ አስተችቶናል። የአንደበታችን አለመገራት በብዙዎች ዘንድ እምነታችን እንዲተችና እንዲነቀፍ መንስኤ እና ምክንያት ሆኖአል። ስለዚህ የአንደበታችንን ጉዳይ እጅግ በአፅንኦት ልንመለከተው ይገባል። በተለይ ከምናለማው በላይ የምናቃጥለው በዝቷል። 

“ነገር ግን አንደበትን ሊገራ ማንም ሰው አይችልም፤ የሚገድል መርዝ የሞላበት ወላዋይ ክፋት ነው።”— ያዕቆብ 3፥8። አንደበታችንን በራሳችን አቅም ልንገራውና ልንቆጣጠረው ባንችልም፣ እግዚአብሔር እራሱ ጠባቂ ያኑርልን። 

  1. ጉዞን ያውካል፦ ያልተጎሰመ አንደበት በሕይወት እያደረግን ያለነውን ማንኛውም ነገር የማወክ ኃይል አለው። 
    አንደበት፦ በተለይ ወሬ ከታከለበት የሌሎችን አቋም የመሸርሸርና የማውረድ አቅም አለው። “ስለ ሰለሉአትም ምድር ክፉ ወሬ ለእስራኤል ልጆች እያወሩ፦ እኛ ዞረን የሰለልናት ምድር የሚኖሩባትን ሰዎች የምትበላ ምድር ናት፤ በእርስዋም ዘንድ ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው።” — ዘኍልቁ 13፥32። 
  2. ከመሪ ያጣላል፦ በተለይ በአንድ ህብረት ውስጥ ያለ አንደበቱ ያልተጎሰመ አካል ሕብረቱን የማናጋትና ከመሪ ጋር የማጋጨት ብቃት አለው። ይህም ሲሆን ዓላማ እና ግብ ከስኬት እንዳይደርስ እንቅፋትና መሠናክልን ያደርጋል። “ምድሪቱንም ሊሰልሉ ሙሴ ልኮአቸው የተመለሱት ሰዎች ክፉ ወሬም ስለ ምድሪቱ እያወሩ በእርሱ ላይ ማኅበሩ ሁሉ እንዲያጕረመርሙ ያደረጉ፥”— ዘኍልቁ 14፥36። “ክፉ ወሬ ያወሩ እነዚያ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት በመቅሠፍት ሞቱ።” — ዘኍልቁ 14፥37። 

አንደበታችንን መጠቀም ያለብን መጥፎ ቃላትን ከመናገር መከልከል ብቻ ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን የሚጠቅመውን ለመናገርም ነው። በመጽሐፍም “ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።”— ኤፌሶን 4፥29። 

ያልተጎሰመ አንደበት፦ አምልኮአችንን፣ እምነታችንን የሚያስነቅፍ፣ የሚያስተች፣ የሚያጎድፍ ነው። ስለዚህ፦ ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ፥ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር፥ እርሱ አምልኮቱ ከንቱ ነው›› በማለት የተናገራቸው ቃላት ባልተገደበ አንደበት ምክንያት የአንድ ሰው የክርስትና ህይወት እና አምልኮ እንዴት ከንቱ ሊሆን እንደሚችል ያመላክታል። ክርስትና ያለ ትህትናና ምግባር ከንቱ በመሆኑ የማንተገብራቸውን ተግባራት በተዋቡ ቃላት ከሽነንና አጅበን በሽንግላ አንደበት በስመ ክርስቲያን ብቻ መኖር የተገባ አይደለም፡፡ “አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው።”— ያዕቆብ 1፥26። 

በሐዋርያው ያዕቆብ እንደገለጸው ከቁጥጥር ውጭ የሆነ አንደበት ወደ ኃጢአት ይመራል፡፡ አንድ ሰው ምላሱን ሳይገታ፣ በክፉ እሳቤ ተነሣስቶ ቃላትን ቢያወጣ በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ እክል ይሆንበታል። አምልኮው፣ አገልግሎቱ እና ልፋቱ ሁሉ መና ይሆናል። እምነት በጎደለውና በሐሰተኛ አንደበት የእውነትን ቃላት ብናወጣ የእግዚአብሔርን ሕግ አለማክበር በመሆኑ የጽድቅ ሳይሆን የኵነኔ ፍርድ ይከተለናል፡፡ “ክፉ ወሬ ያወሩ እነዚያ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት በመቅሠፍት ሞቱ።” — ዘኍልቁ 14፥37።

በመጨረሻም፦
ስለዚህ የሰውነት አካለለችን መካከል አንደበት የማንነት መገለጫ ነው። ልንጠብቀው የሚገባ የሰውነታችን ክፍል ነው። ካልጠበቅነው ውርደታችንን የሚያፈጥን የሰውነታችን ክፍል ነው ።እግዚአብሔር የሚከብርበት እኛም የምንከብርበት ወይንም ከክብር የምንዋረድበት የሰውነታችን አካል ማለት ነው። “ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው፤ የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ።”
  — ምሳሌ 18፥21። 

“አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ።” — መዝሙር 141፥3። 

“አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።” — መዝሙር 19፥14። 

እግዚአብሔር ይባርካችሁ!
አገልጋይ በረከት ሱላሞ ሱጌቦ

ያልተጎሰመ አንደበት

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ


tongue

ያልተጎሰመ አንደበት

“አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ።”— መዝሙር 34፥13። 

በአለም ላይ የተደረጉ የትኛውም አይነት ጦርነቶች በቅድሚያ ውጊያን የጀመሩት በዘመናቸው በነበሩት የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም በአንደበት ነው። ክፉ አንደበት የጠብ ጫሪነትን ሚና በከፍተኛ ደረጃ የምትወጣ የክፉ አለም ተምሳሌት ነች። የጦርነት ክተት ይሁን አዋጅ በነጋሪት ጉሰማ ሲታወጅ አንደበት የጦርነትን መጀመር ፋና ወጊና ፈር ቀዳጅ አንደበት ነው። በአንደበት በትንሽ ምላስ የተጫረ የጦርነት ምላጭ ተኩስ የተጀመረው በዚህ በአንደበት አለም ነው። 

በክርስትናውም አለም እንዲሁ ያልተጎሰመ አንደበት ሥራው ይኸው ሲሆን በተለይ በወንድማማች መካከል ጠብን በመዝራት የሚታወቀው ይኸው ያልተገራው አንደበት ነው። በተለይ በዚህ ባለንበት ዘመን እጅግ ብዙ አገልጋዮች በድብደባና በዱላ ከመሰበር በላይ በአንደበት የተሰበሩት ኅልቁ መሳፍርት ናቸው። 

በብሉይ ኪዳን ዘመን እንኳን ስንመለከት ሙሴ ከላካቸው አስራ ሁለቱ ሰላዮች የአስሩ መረጃ የሕዝበ እስራኤልን ልብ ያቀለጠ መረጃ ነበር። በተለይ ከአፋቸው የሚወጣው ንግግር የሕዝቡ ልብ እስኪቀልጥ ድረስ እና በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ እስኪነሱ ድረስ ያደረሰን ተገቢ ያልሆነን መረጃ ይዘው በመምጣት የህዝብን ልብና ጉዞ አውከዋል። “ከእኔ ጋር የወጡ ወንድሞቼ ግን የሕዝቡን ልብ አቀለጡ፤ እኔ ግን አምላኬን እግዚአብሔርን ፈጽሜ ተከተልሁ።” — ኢያሱ 14፥8። 

የብዙዎች ሕይወትና አገልግሎት እንዲሁም ሩጫቸው የተቃጠለውና የተመታው በአንደበት አለም በተደረገው ጦርነት ነው። በሰውነታችን ላይ ካሉት ብልቶቻችን ወይም የሰውነት ክፍሎቻችን መካከል እጅግ አደገኛው አካል ወይም ብልት አንደበት ነው። አጥንት እስኪሰበር የሚያደርስን ክፋት የተሞላ መርዛማ ነገር ነው። 

“እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል።”— ያዕቆብ 3፥5። 

“አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።”— ያዕቆብ 3፥6።


በተለይ በመፅሐፍ ቅዱሳችን ስለ አንደበት የተነገረው ቃል እጅግ አሉታዊ በሆነ መንገድ የተገለጸው ነው። ስለ አንደበት በዝርዝር በማንነቱና በባህሪው የተገለጠበት መንገድ፦
1. ትንሽ ብልት
2. በታላላቅ ነገር ይመካል
3. እሳት 
4. ዓመፀኛ አለም
5. ሥጋን የሚያሳድፍ
6. ሩጫን የሚያቃጥል
7. በገሃነምም የሚቃጠል እንደሆነ በግልፅ ተቀምጧል። 

በተለይ በነህምያ እና በዕዝራ ዘመን የፈረሰችውን እየሩሳሌምን በሚጠግኑበት ጊዜ በዙሪያቸው የነበሩት ጠላቶቻቸው የመጀመሪያውን ጦርነት የጀመሩት በአንደበት ጦርነት በሚያናንቅና በሚያጥላላ ንግግር ነው። “አሞናዊውም ጦብያ በአጠገቡ ቆሞ፦ በድንጋይ በሚሠሩት ቅጥራቸው ላይ ቀበሮ ቢመጣበት ያፈርሰዋል አለ።” — ነሀምያ 4፥3። አንደበት የዚህን ያህል ውስጥን የሚያበግን ንግግርን አፍልቆ ስሜትን ይነካል። ለዚህ ነው ነህምያ በምላሹ፦ “አምላካችን ሆይ፥ ተንቀናልና ስማ፤ ስድባቸውን በራሳቸው ላይ መልስባቸው በምርኮ አገር ለብዝበዛ አሳልፈህ ስጣቸው።” — ነሀምያ 4፥4። “በደላቸውንም አትክደን፥ ኃጢአታቸውም ከፊትህ አይደምሰስ፤ በሠራተኞች ፊት አስቆጥተውሃልና።” — ነሀምያ 4፥5። 

የአለማውያኑ ንግግር ይህን ያህል ላይጎዳ ይችላል፣ ምክንያቱም የባህሪያቸው ስለሆነ ቦታ ላንሰጠው እንችል ይሆናል። ሆኖም ግን በእኛ በክርስቲያኖች መካከል የሚደረገው የአንደበት ላይ ጦርነቶች በብዙ አኅዛብ መካከል መሳለቂያ እስከመሆን ደርሰናል። በተለይ በመፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ላይ ያለን የሰፋ ልዩነትና የምንሰጣጣቸው ምላሾች በብዙዎች ዘንድ አስተችቶናል። የአንደበታችን አለመገራት በብዙዎች ዘንድ እምነታችን እንዲተችና እንዲነቀፍ መንስኤ እና ምክንያት ሆኖአል። ስለዚህ የአንደበታችንን ጉዳይ እጅግ በአፅንኦት ልንመለከተው ይገባል። በተለይ ከምናለማው በላይ የምናቃጥለው በዝቷል። 

“ነገር ግን አንደበትን ሊገራ ማንም ሰው አይችልም፤ የሚገድል መርዝ የሞላበት ወላዋይ ክፋት ነው።”— ያዕቆብ 3፥8። አንደበታችንን በራሳችን አቅም ልንገራውና ልንቆጣጠረው ባንችልም፣ እግዚአብሔር እራሱ ጠባቂ ያኑርልን። 

  1. ጉዞን ያውካል፦ ያልተጎሰመ አንደበት በሕይወት እያደረግን ያለነውን ማንኛውም ነገር የማወክ ኃይል አለው። 
    አንደበት፦ በተለይ ወሬ ከታከለበት የሌሎችን አቋም የመሸርሸርና የማውረድ አቅም አለው። “ስለ ሰለሉአትም ምድር ክፉ ወሬ ለእስራኤል ልጆች እያወሩ፦ እኛ ዞረን የሰለልናት ምድር የሚኖሩባትን ሰዎች የምትበላ ምድር ናት፤ በእርስዋም ዘንድ ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው።” — ዘኍልቁ 13፥32። 
  2. ከመሪ ያጣላል፦ በተለይ በአንድ ህብረት ውስጥ ያለ አንደበቱ ያልተጎሰመ አካል ሕብረቱን የማናጋትና ከመሪ ጋር የማጋጨት ብቃት አለው። ይህም ሲሆን ዓላማ እና ግብ ከስኬት እንዳይደርስ እንቅፋትና መሠናክልን ያደርጋል። “ምድሪቱንም ሊሰልሉ ሙሴ ልኮአቸው የተመለሱት ሰዎች ክፉ ወሬም ስለ ምድሪቱ እያወሩ በእርሱ ላይ ማኅበሩ ሁሉ እንዲያጕረመርሙ ያደረጉ፥”— ዘኍልቁ 14፥36። “ክፉ ወሬ ያወሩ እነዚያ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት በመቅሠፍት ሞቱ።” — ዘኍልቁ 14፥37። 

አንደበታችንን መጠቀም ያለብን መጥፎ ቃላትን ከመናገር መከልከል ብቻ ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን የሚጠቅመውን ለመናገርም ነው። በመጽሐፍም “ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።”— ኤፌሶን 4፥29። 

ያልተጎሰመ አንደበት፦ አምልኮአችንን፣ እምነታችንን የሚያስነቅፍ፣ የሚያስተች፣ የሚያጎድፍ ነው። ስለዚህ፦ ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ፥ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር፥ እርሱ አምልኮቱ ከንቱ ነው›› በማለት የተናገራቸው ቃላት ባልተገደበ አንደበት ምክንያት የአንድ ሰው የክርስትና ህይወት እና አምልኮ እንዴት ከንቱ ሊሆን እንደሚችል ያመላክታል። ክርስትና ያለ ትህትናና ምግባር ከንቱ በመሆኑ የማንተገብራቸውን ተግባራት በተዋቡ ቃላት ከሽነንና አጅበን በሽንግላ አንደበት በስመ ክርስቲያን ብቻ መኖር የተገባ አይደለም፡፡ “አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው።”— ያዕቆብ 1፥26። 

በሐዋርያው ያዕቆብ እንደገለጸው ከቁጥጥር ውጭ የሆነ አንደበት ወደ ኃጢአት ይመራል፡፡ አንድ ሰው ምላሱን ሳይገታ፣ በክፉ እሳቤ ተነሣስቶ ቃላትን ቢያወጣ በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ እክል ይሆንበታል። አምልኮው፣ አገልግሎቱ እና ልፋቱ ሁሉ መና ይሆናል። እምነት በጎደለውና በሐሰተኛ አንደበት የእውነትን ቃላት ብናወጣ የእግዚአብሔርን ሕግ አለማክበር በመሆኑ የጽድቅ ሳይሆን የኵነኔ ፍርድ ይከተለናል፡፡ “ክፉ ወሬ ያወሩ እነዚያ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት በመቅሠፍት ሞቱ።” — ዘኍልቁ 14፥37።

በመጨረሻም፦
ስለዚህ የሰውነት አካለለችን መካከል አንደበት የማንነት መገለጫ ነው። ልንጠብቀው የሚገባ የሰውነታችን ክፍል ነው። ካልጠበቅነው ውርደታችንን የሚያፈጥን የሰውነታችን ክፍል ነው ።እግዚአብሔር የሚከብርበት እኛም የምንከብርበት ወይንም ከክብር የምንዋረድበት የሰውነታችን አካል ማለት ነው። “ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው፤ የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ።”
  — ምሳሌ 18፥21። 

“አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ።” — መዝሙር 141፥3። 

“አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።” — መዝሙር 19፥14። 

እግዚአብሔር ይባርካችሁ!
አገልጋይ በረከት ሱላሞ ሱጌቦ

ሥራ ፈት አንሁን

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

ሥራ ፈት አንሁን

ሥራ ፈትነት ከምሁራን አንደበት

ሥራ ፈትነትን ከማብራራት አስቀድሜ ነገሬን በዚህ ሥራ በሚለው ጉዳይ ላይ አንድ ምሁር የተናገሩትን ትንሽ ቁም ነገር አዘል ጉዳይ ጠቆም ላድርግና ወደ ተነሳሁበት ሃሳብ ትንሽ ቆየት ብዬ ልመለስ፡፡ ይህ ምሁር ቮልቴር የሚባል ፈረንሳዊ ሊቅና ፈላስፋ ሲሆን ስለ ሥራ የተናገረውን ላንሳ፡- ቮልቴር ሲናገርሥራ ከሶስት ነገሮች የሰውን ልጅ ይጠብቃል ብሎ ይናገራል፡፡

  1. ከድባቴ ወይም ከድብርት
  2. ከመጥፎ እኩይ ተጋባርና ድርጊት
  3.  ከድህነት፤ ከችግር ይጠብቃል ይከላከላል በማለት ሙያዊ ምክሩን ይሰጣል፡፡

እውነታው ላይ ተመርኩዘን ስናየውና ስናጤነው ቮልቴር የተናገረው እጅገ እውነት ነው፡፡ በምድራችን አሁን ላይ የምናየው የስራ ፈትነት ካመጣቸው አሉታዊ ችግሮች በይበልጥ ተስተውለው የሚታዩት እነዚህ ናቸው፡፡

ዛሬም በቤተክርስቲያን ውስጥ ከዚህ የተለየ ችግር እያየን አይደለም፡፡ ጉዳዩ የአለማዊ ዕውቀት እና የመንፈሳዊ እውቀት ብለን እንፈርጀው እንጂ በስው ልጅ ላይ እየታየ ያለው ተመሳሳይ ነገር ነው፡፡ ዛሬ ላይ መንግስታትን እያሳሰበ እና እየተፈታተን ያለው ነገር ቢኖር የሥራ ፈት ቁጥር ማሸቀቡና ለዚህም መፍትሄ ማጣቱ ነው፡፡

Read more: ሥራ ፈት አንሁን

የተገለጠው የእግዚአብሔር ጸጋ

Details
Written by: Mekete Sugebo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የእግዚአብሔር ጸጋ

Read more: የተገለጠው የእግዚአብሔር ጸጋ

በክርስቶስ የተገኘ ልጅነት እና ትሩፋቶቹ

Details
Written by: Mekete Sugebo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የቀደመው ታሪክና ማንነት የተሻረበት፣ ቀድሞ መታወቂያ የነበረው ማንነት ሙሉ በሙሉ የተወገደበት፣ ማዕረግ ያልነበረን ባለማዕረግ የሆንበት፣ ይህም በአንዱ በክርስቶስ በእግዚአብሔር ልጅ ያገኘነው ልጅነት ነው።

Read more: በክርስቶስ የተገኘ ልጅነት እና ትሩፋቶቹ

የምትሰማው ድምጽ

Details
Written by: Mekete Sugebo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 17

አሰላለፍሀን ቀይር፣

ፍልስጤም እንደ ተሰለፈ አትሰለፍ፣ ፍልስጤም እንደ ተከማቸ አትከማች፤

Read more: የምትሰማው ድምጽ

የጌታ ደስታ

Details
Written by: Mekete Sugebo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

ዳይመንሽን
እንደ ቤተ ክርስቲያን ወይም እንደ ግለሰብ አዳዲስ ዳይሜንሽኖች በታናናሽ ምልክቶች ይጀምራሉ።
አዲስ ምልክት ካየህ አዲስ ዳይሜንሽን እየተጀመረ ነው ማለት ነው።

Read more: የጌታ ደስታ

  1. እግዚአብሔር ከስምህ በላይ ነው
  2. እግዚአብሔር ይግነንባችሁ
  3. ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም
  4. ብድራት ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉት

Subcategories

ከመጽሐፍት ዓለም

Page 1 of 3

  • 1
  • 2
  • 3
  • የታጠቀ ትውልድ
  • የትውልድ አደራ
  • እስክንድሮሶች
  • ዲዮጥራጢስ
  • መሰረተ እምነት (2)

Article Categories

  • Literature/ስነ-ጽሑፍ
  • Gospel Thoughts / የወንጌል አስተምህሮ
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
  • Testimony/ምስክርነት
  • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን

Login Form

  • Forgot your password?
  • Forgot your username?
Copyright © 2026 yegizewkal. All Rights Reserved.