yegizewkal
ቃልህ ተገኝቶአል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ፥ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ። ትንቢተ ኤርምያስ 15፥16

  • Home/መነሻ ገጽ
  • Gospel Thoughts/የወንጌል አስተምህሮ
    • ነገረ ድነት/Salvation
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
    • Literature/ስነ-ጽሑፍ
    • ከመጽሐፍት ዓለም
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን
    • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Testimony/ምስክርነት
  • ማስታወቂያ/Advertisement
  1. You are here:  
  2. Home
  3. The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

በመከራ ውስጥ የሚፀና ማንነት

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

በመከራ ውስጥ የሚፀና ማንነት

“በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።” — ዮሐንስ 16፥33።

በአለም ስላለን ብቻ እኛ ክርስቲያኖች መከራ ይደርስብናል ማለቱ ተላላነት ነው፣ በአለም መኖሩ ሳይሆን ክርስቲያን መከራ የመጣበት በአለም ሳለን በእውነት በክርስቶስ ስላለን ነው። በእርግጥ የክርስቶስ ተከታይ ክርስቲያን መባሉ እንዳለ መከራ ቢያመጣም በእርሱ ካለን፣ እንደ ቃሉ ፈቃድ ስንኖር፣ የቃሉን ፈቃድ ስንፈፅም፣ ቃሉን ስንተገብር፣ የኃጢአትን መንገድ ጠልተን በክርስቶስ መንገድ መሄድ በእነዚህ ምክንያት እጅግ የበዛ መከራ መድረሱ አይቀሬ ነው።

በእርግጥ መከራ ፅናትን፣ ትዕግስትን፣ አቋምን የሚፈታተን ቢሆንም በፈተና ውስጥ መፅናቱ የመጨረሻ ዋጋው እጅግ የከበረ ነው። መከራ  በዋናነት ከቆምንበት አቋም መጣል አሊያም ማስጣል፣ ከእግዚአብሔርም ጋር የነበረንን ብርቱ ቁርኝትና ግንኙነት ማበላሸት አሊያም ማቋረጥ ነው።

Read more: በመከራ ውስጥ የሚፀና ማንነት

በሚበልጥ ክብር መገለጥ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

በሚበልጥ ክብር መገለጥ

በዘመናችን እየታየ ያለው እንቅስቃሴ በተለይ ከእግዚአብሔር ቃል አኳያ የምናያቸው አብዛኞቹ ነገሮች አሳዛኝ፣ ልብ ሰባ፣ አስከፊ እና ፀያፍ ናቸው። ክርስቲያን እንደ ክርሰቲያንነት የሚታይበት የሌለው፣ እግዚአብሔርን እከተላለሁ የሚል እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የማይሄድ የበዛበት ዘመን፣ ከተግባራዊ ክርስትና ይልቅ አፋዊ ክርስቲያን እና ክርስትና እያየን ያለንበት ዘመን፣ ለአብነት ምስክር መሆን የማንችል፣ ለሌሎች ለሚያምኑም ይሁን ለማያምኑ መልካም ምስክርነት የሌለን ተላላዎች ሆነን እየታየን ነው። ይህ ማንነት ግን ጨርሶ እግዚአብሔራዊ እና ክርስቶሳዊ እና ክርስቲያናዊ አይደለም። ከጥንት የነበሩ በመጽሐፍ ቅዱስ ያየናቸው የእግዚአብሔር ሰዎች በዚህ ማንነት ተገልጠው አናያም፣ ይልቁኑ መንግስታትን በጽድቅ ኖረው፣ አገልግለው ድል ነስተው እግዚአብሔርን አስከብረው አልፈዋል። በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ይሁኑ በእግዚአብሔር ነገር እና ጉዳይ አይደራደሩም፣ እስከመጨረሻው በእግዚአብሔር ጉዳይ ይጋፈጣሉ፣ ይወራረዳሉ በመጨረሻም በእግዚአብሔር ያሸንፋሉ። በሚበልጥ ክብር፣ በሚበልጥ በእግዚአብሔር ኃይልና ክብር መገለጥ በዘመኑ ላይ ባለው ክፋት፣ አመፅ፣ ከእግዚአብሔር በተቃራኒ በቆመ ላይ አይሎ፣ ረግጦ፣ አሸንፎና አጥፍቶ በበላይነት በመቆም የእግዚአብሔርን ስም እንዲገን በማድረግ በገዢነት ለመቆየት ወሳኙ ነው።

Read more: በሚበልጥ ክብር መገለጥ

አልባሾችህን ጠንቅቀህ እወቅ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

አልባሾችህን ጠንቅ ቀህእወቅ 

በአገልግሎት ዘመን እጅግ በብዙ ልንጠነቀቅ የሚገባው ነገር ቢኖር በአገልግሎት ዙሪያ አብረውኝ ያሉት እነማን ናቸው፣ አቋማቸውስ እንዴት ነው፣ አብረውኝ መከራ የሚቀበሉ ናቸው ወይስ መከራ አምጪ? በእርግጥ በአገልግሎት ዘመን እጅግ የቅርብ ናቸው የምንላቸው የመከራ አምጪ አሊያም አስመጪ ሊሆኑ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ አብረኸኝ መከራ ተቀበል ብለን ልንጠራው የማንችል ሊኖር ይችላል፣ አብረኸኝ በጎ ወታደር ሆነህ መከራ ተቀበል የምንለው ላይኖር ይችላል። ብቻ ግን አቅምንና አቋምን ሳያስነኩ መዝለቁ እና የወንጌሉ ሥራ እንዲቀጥል እግዚአብሔር በጎኔ ቆሞ አበረታኝ እንዳለው ጳውሎስ ከሰው በላይ ሊረዳው የሚችል እግዚአብሔር እንዳለ ጠንቅቆ የሚያውቅ ሲሆን፣ የሚረዱት ወንድሞች ባይኖሩትም፣ ለምን መጣህ የልብህን ኩራት እናውቃለን ቢሉት ዳዊት ይህስ ትልቅ ስራ አይደለምን ማለቱ፣ ጎልያድን በተገዳደርከው በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ ማለቱ ረዳቱ እግዚአብሔር እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። ለራእይህ ዘላቂነት፣ ታማኝ ተደርገህ ለተቆጠርክበት አገልግሎትህ መቃናት፣ ለአገልግሎትህ ድጋፍ ሰዎች ወሳኝ መሆናቸው እሙን ነው። ሆኖም ግን አጠገብህ ያሉ ሁሉ ለራእይህ፣ ለመጪው አገልግሎትህ መጥፋት አልያም መሳካት አስተዋጽኦ ሊኖራቸው ይችላል።

Read more: አልባሾችህን ጠንቅቀህ እወቅ

የትውልድ አደራ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

 

የትውልድ አደራ

የትውልድ ባለአደራነትን መወጣት

አደራ ለአንድ የተወሰነ ተግባር እና ክዋኔ ወይም ግዴታ ለአንድ ሰው ሃላፊነት ወይም ስልጣን መስጠት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን፣ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት እና በኃላፊነት እንዲወጣ እምነትን መጣል ሲሆን፣ አደራ የአደራን ተግባር በአደራ፣ በመተማመን እና በአደራ የተሰጠው ሰው አቅም ላይ በማመን ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይችላል። 

 

አደራን የመወጣት እና አደራን ከግብ ማድረስ እንዴት ያለ መታደል ነው። በተለይ የትውልድን አደራ ተቀብሎ ትውልድ በመልካም መንገድ የእግዚአብሔርን ሕግ ተከትሎ እንዲሄድ አድርጎ እና በዚህም ፍሬን ማየት እንዴት እጅግ ያስደስታል። 

Read more: የትውልድ አደራ

የተፅእኖ ሰው

Details
Written by: BEREKET SULAMO SUGEBO
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የተፅእኖ ሰው

እነርሱ በእምነት መንግስታትን ድል ነሡ ጽድቅን አደረጉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ

ዕብራውያን 11፡33

Read more: የተፅእኖ ሰው

ያልተጎሰመ አንደበት

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ


tongue

ያልተጎሰመ አንደበት

“አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ።”— መዝሙር 34፥13። 

በአለም ላይ የተደረጉ የትኛውም አይነት ጦርነቶች በቅድሚያ ውጊያን የጀመሩት በዘመናቸው በነበሩት የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም በአንደበት ነው። ክፉ አንደበት የጠብ ጫሪነትን ሚና በከፍተኛ ደረጃ የምትወጣ የክፉ አለም ተምሳሌት ነች። የጦርነት ክተት ይሁን አዋጅ በነጋሪት ጉሰማ ሲታወጅ አንደበት የጦርነትን መጀመር ፋና ወጊና ፈር ቀዳጅ አንደበት ነው። በአንደበት በትንሽ ምላስ የተጫረ የጦርነት ምላጭ ተኩስ የተጀመረው በዚህ በአንደበት አለም ነው። 

በክርስትናውም አለም እንዲሁ ያልተጎሰመ አንደበት ሥራው ይኸው ሲሆን በተለይ በወንድማማች መካከል ጠብን በመዝራት የሚታወቀው ይኸው ያልተገራው አንደበት ነው። በተለይ በዚህ ባለንበት ዘመን እጅግ ብዙ አገልጋዮች በድብደባና በዱላ ከመሰበር በላይ በአንደበት የተሰበሩት ኅልቁ መሳፍርት ናቸው። 

Read more: ያልተጎሰመ አንደበት

ሥራ ፈት አንሁን

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

ሥራ ፈት አንሁን

ሥራ ፈትነት ከምሁራን አንደበት

ሥራ ፈትነትን ከማብራራት አስቀድሜ ነገሬን በዚህ ሥራ በሚለው ጉዳይ ላይ አንድ ምሁር የተናገሩትን ትንሽ ቁም ነገር አዘል ጉዳይ ጠቆም ላድርግና ወደ ተነሳሁበት ሃሳብ ትንሽ ቆየት ብዬ ልመለስ፡፡ ይህ ምሁር ቮልቴር የሚባል ፈረንሳዊ ሊቅና ፈላስፋ ሲሆን ስለ ሥራ የተናገረውን ላንሳ፡- ቮልቴር ሲናገርሥራ ከሶስት ነገሮች የሰውን ልጅ ይጠብቃል ብሎ ይናገራል፡፡

  1. ከድባቴ ወይም ከድብርት
  2. ከመጥፎ እኩይ ተጋባርና ድርጊት
  3.  ከድህነት፤ ከችግር ይጠብቃል ይከላከላል በማለት ሙያዊ ምክሩን ይሰጣል፡፡

እውነታው ላይ ተመርኩዘን ስናየውና ስናጤነው ቮልቴር የተናገረው እጅገ እውነት ነው፡፡ በምድራችን አሁን ላይ የምናየው የስራ ፈትነት ካመጣቸው አሉታዊ ችግሮች በይበልጥ ተስተውለው የሚታዩት እነዚህ ናቸው፡፡

ዛሬም በቤተክርስቲያን ውስጥ ከዚህ የተለየ ችግር እያየን አይደለም፡፡ ጉዳዩ የአለማዊ ዕውቀት እና የመንፈሳዊ እውቀት ብለን እንፈርጀው እንጂ በስው ልጅ ላይ እየታየ ያለው ተመሳሳይ ነገር ነው፡፡ ዛሬ ላይ መንግስታትን እያሳሰበ እና እየተፈታተን ያለው ነገር ቢኖር የሥራ ፈት ቁጥር ማሸቀቡና ለዚህም መፍትሄ ማጣቱ ነው፡፡

Read more: ሥራ ፈት አንሁን

የተገለጠው የእግዚአብሔር ጸጋ

Details
Written by: Mekete Sugebo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የእግዚአብሔር ጸጋ

  • ሰዎችን ሁሉ የሚያድን ነው።
  • ሃጢአተኝነትንና ዓለማዊ ምኞትን የሚያስክድ ነው።
  • የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ እንዴት እንደምንጠብቅ የሚያስተምር ነው።
  • ራሳችንን መግዛት የሚያስተምር እና የሚያሰለጥን ነው።
  • በጽድቅ መኖርን የሚያስተምር ነው።
  • እግዚአብሔርን መምሰል የሚያስተምር ነው።

    Read more: የተገለጠው የእግዚአብሔር ጸጋ

በክርስቶስ የተገኘ ልጅነት እና ትሩፋቶቹ

Details
Written by: Mekete Sugebo
Category: The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ

የቀደመው ታሪክና ማንነት የተሻረበት፣ ቀድሞ መታወቂያ የነበረው ማንነት ሙሉ በሙሉ የተወገደበት፣ ማዕረግ ያልነበረን ባለማዕረግ የሆንበት፣ ይህም በአንዱ በክርስቶስ በእግዚአብሔር ልጅ ያገኘነው ልጅነት ነው።

Read more: በክርስቶስ የተገኘ ልጅነት እና ትሩፋቶቹ

  1. የምትሰማው ድምጽ
  2. የጌታ ደስታ
  3. እግዚአብሔር ከስምህ በላይ ነው
  4. እግዚአብሔር ይግነንባችሁ

Subcategories

ከመጽሐፍት ዓለም

Page 1 of 3

  • 1
  • 2
  • 3
  • EECFNA
  • በመከራ ውስጥ የሚፀና ማንነት
  • በሚበልጥ ክብር መገለጥ
  • አልባሾችህን ጠንቅቀህ እወቅ
  • የይሁዳ መልዕክት

Article Categories

  • Literature/ስነ-ጽሑፍ
  • Gospel Thoughts / የወንጌል አስተምህሮ
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
  • Testimony/ምስክርነት
  • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን
Copyright © 2026 yegizewkal. All Rights Reserved.