yegizewkal
ቃልህ ተገኝቶአል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ፥ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ። ትንቢተ ኤርምያስ 15፥16

  • Home/መነሻ ገጽ
  • Gospel Thoughts/የወንጌል አስተምህሮ
    • ነገረ ድነት/Salvation
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
    • Literature/ስነ-ጽሑፍ
    • ከመጽሐፍት ዓለም
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን
    • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Testimony/ምስክርነት
  • ማስታወቂያ/Advertisement
  1. You are here:  
  2. Home
  3. The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
  4. Literature/ስነ-ጽሑፍ

Literature/ስነ-ጽሑፍ

የታጠቀ ትውልድ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

የታጠቀ ትውልድ

 

በዘመናት ሁሉ በየትኛውም የአገዛዝ ስርአት አይነት ውስጥ መንግስታት፣ የመንግስታት መሪዎች ትልቁ ስጋታቸው እና ፍርሃታቸው የወጣቱ ትውልድ ቁጥር ነው። የቁጥራቸውና የብዛታቸው ማነስ ስጋትን ሲያጭር፣ የቁጥራቸው መብዛት የነገ ተስፋ ፍንትው ብሎ ይታያቸዋል። የቁጥራቸው መብዛት የነገ የደህንነት ስጋታቸውን በእጅጉ ይቀንሰዋል፣ ብቁና የጠነከረ ትውልድ መኖሩ ነገ ለሚመጣው አሉታዊ ነገር ምላሽ የሚሰጥበት አቅም እንዳለው ፍርሃትን ይቀንስለታል። 

ብዙውን ጊዜ ተፃራሪ መንግስታት አንዱ አንዱን መሠለል የዘወትር ሥራቸው ሲሆን ይህም ምን ያህል ለውትድርና ብቁ የሆነ ወጣት አለ? የመጠነ ሐብትስ ምን ያህል ነው? ተባብሎ መፈታተሹና አንዱ አንዱን መሠለሉ የአቅምን ሁኔታ ለማደርጀትና ለማጎልበት ግብዓት ይሆናቸዋል። 

Read more: የታጠቀ ትውልድ

ያልተጎሰመ አይን

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ


ያልተጎሰመ አይን

እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ እነዚህም ዝሙትና ርኩሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው፤ ቆላስይስ 3:5።

የሰው ልጅ ነገርን ከሚረዳበትና ከሚለይበት ነገሮች መካከል አንዱ አይን መሆኑ የማይካድ ሃቅ ነው። አበው በብሂላቸው እንኳኖ ሲያስቀምጡ "ነገር በአይን ይገባል" የሚሉት ብሂል  እውነታው የማያከራክርና የማያወላዳ ነው። አንዳንዴም ነገር እውነት ለመሆኑና ላለመሆኑ "አይኔን እያየህ አውራ" የሚሉትም እንዲሁ ነው። ነገር በአይን ይገባል፣ ይዘልቃልም። እንግዲህ ይህን ያህል ካልን እና ቢበቃ እንደው ያልተጎሰመ አይን ክፋቱን እና በህይወት በተለይ በእግዚአብሔር ዘንድ ባለን ምልልስ እና የክርስትና ህይወታችን ላይ የሚያመጣውን አሉታዊ ጣጣን እንመልከት። 

በተለይ ሥራ እያላቸው ሥራ ፈትተው የሚገኙ ሰዎች አይናቸው የማይፈለግን ነገር በማየት ተገቢ ያልሆነን ነገር በማድረግ ይታወቃሉ። ሥራ ያለው ሁልጊዜም ትኩረቱና እይታው ሥራ ላይ ብቻ ነው፣ በተለይ ለኃጢአት ጊዜና ቦታ ጨርሶውኑ የላቸውም። 

Read more: ያልተጎሰመ አይን

ጊዜ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

                          ጊዜ

መግቢያ

 ጊዜ እንደ ምንመገበው ምግብ፣ እንደምንጠጣው ውሃ እና እንደ  ምንተነፍሰው አየር ሁሉ ዋጋ  ያለውና በሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ትኩረት የሚያሻው ከእግዚአብሔር የተሠጠን ዕድል ነው። የሰው ልጅ በእያንዳንዱ የሕይወት እንቅስቃሴ እና ኑሮ  በሕይወት እስካለ ድረስ እድሜው ተወስኖ እና ተመጥኖ  የተሰጠው የጊዜ ልኬት ገደብ አለ። 

ላወቀ፣ ለተረዳና ለገባው ጊዜ ለሰው ልጅ ውዱ ሀብት ነው። ለሰው ልጅ ጊዜ ሲሰጥም ተመጥኖና ተወስኖ እንጂ እንደ አሸዋ የሚዘገን፣ ተዘግኖም የሚሰጥም የተሰጠም፣ የሚቸር የተቸረም አይደለም፣ ገደብ አለውና። አበው ሲናገሩ እንኳን "እድሜና ጤና ይስጠን እንጂ ብዙ እናያለን" የማንሠራውና የማናየው የለም የሚሉት በዚህ ምክንያት ነው። የጊዜን ብርታትና ጥንካሬንም ሲገልጹ "ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል"፤ ይህ ማለት ምን ያህል የጊዜን ሃያልነት እንደሚያውቁ መረዳት ሲቻል፣ በተጨማሪም ጉብዝናውን ለመግለፅ "ጊዜ ጎበዙ" በማለትም የውዳሴ ያህል በማሞካሸት ይገልጹታል። በእድሜ ዘመን የዕድሜ ልኬት ለሰው ልጅ የመኖሪያ ጣሪያው ለእያንዳንዱ ሰው የተሰጠው የጊዜ ገደብ ማለቂያ አለው። ልኬቱና መጠኑም የሚታወቀው ሲሰጥ ሳይሆን ሲያበቃና ሲያከትም ሲያልቅ ብቻ ነው። የጊዜ ዋጋንም የምናውቀው የዚያን ጊዜ ብቻ ነው። 

Read more: ጊዜ

ትጋት

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

 

------------------------------------------------------------------------------------------

 

 

ትጋት

“ለሰው የከበረ ሀብት ትጋት ነው”

(ምሳ. 12፥27)።

መግቢያ

በዚህ ዓለም ላይ ፍሬያማ ሠራተኛ ወይም ውጤታም ሠራተኛ የምንለው ሰው ለውጤታማነትና ለፍሬያማ ሠራተኝነት ከሚያበቃው ዋነኛ ነገር አንዱ ትጋት እንደሆነ የማይካድ ሐቅ ነው፡፡ የሚተጉ ሰዎች ዋነኛ መገለጫ ባህሪያቸው ለጊዜ ያላቸው የጠለቀ አመለካከት እና ዋጋ ትጋታቸውን ጨምሮላቸው ውጤታማ መሆነቸው ነው፡፡

የሚተጉ ሰዎች ሌላኛው ባህሪያቸው እጅግ ትዕግሰተኛ መሆናቸውና ሁልጊዜ ላለሙት ግብና ስኬት ዘወትር በትዕግስት እና እጅግ ብልሃት በታከለበት መንገድ ሥራን መከወናቸው ሲሆን ጥረታቸውን ለቅፅበት ያህል አለማቋረጣቸው ለትጋታቸው ግብዓት ሆኖ ተጠቅመው ግባቸው ላይ ይደርሳሉ፡፡

ትጋት ብዙ ጥረትን፤ የጊዜ አጠቃቀምነ፤ ትዕግስተኝነትን፤ መቋቋምን፤ ግብን ዓላማን ውጤትን ትኩረት አድርጎ የሚነሳ የሥራ መከወኛ ኃይል እና ብርታት ነው፡፡ ትጋት የጊዜን አጠቃቀም፤ ለጊዜ ዋጋን የሚሰጥ፤ ጊዜ እንዲባክን የማይፈልግ፤ ከሁሉ በላይ ለስንፍና ቦታ የሌለው አንዳች ኃይል ነው፡፡

ትዕግስት ከሌለ ትጋት የለም፤ ትጋት ከሌለ ስኬት የለም፤ ስኬት ከሌለ ቀጣይ ምዕራፍ አይታሰብም፡፡ ስለዚህ ትዕግስትና ትጋት በእጅጉ ተሰናስለው የሚኖሩ ነገሮች ናቸው፡፡

 

ትጋት ማለት በግሪክ SPODAZO (ስፓዳዞ) ሲሆን ትርጉሙም ፍጥነትን መጠቀም፣ ጥረት ማድረግ ሲሆን የማይበርድ ጥረት፣ በጽናት የሚደረግ ሥራ፣ በሙሉ ኃይልና ጥንቃቄ የሚደረግ ሥራ ማለት ነው። እንዲሁም የአንድ ሰው ጽናትና ጥንቃቄ የተሞላበት፣ ጠንካራ፣ ጽናት እና ቀጣይነት ያለው ስራ እንዲያከናውን ያስችለዋል። ትጉ ሰዎች ሥራን የመፈጸም አቅም አላቸው!

በክርስትና እምነት ውስጥ እጅግ የሚፈለግ እና የሚመከር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም  ተደጋግሞ ከተጠቀሱት ቃላቶች አንዱ ትጋት ነው። ይህም የሚያሳየው ትጋት ለሰው ልጅ ምን ያህል ወሳኝና አስፈላጊ እንደሆነ ነው። የምሳሌ መጽሐፍ ጸሐፊው ሰለሞን ትጋት ለሰው ልጅ የከበረ ሀበት እንደሆነ ይናገራል። “ለሰው የከበረ ሀብት ትጋት ነው” (ምሳ. 12፥27)።

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ትጋት የተሰጠንን በረከት የምንወርስበት አቅም እና ጉልበት ነው፡፡ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገብ ቃላት መሠረት ትጋት መንቃትን፣ ቸል አለማለትን፣ እንዲሁም ሳይታክቱ ያለ እንቅልፍ እና ድካም መጠበቅ ነው። በክርስትና አስተምህሮ ትጉህ መሆን ማለት ለእግዚአብሔር ባለን ቁርጠኝነት ውስጥ ሀላፊነት፤ ዘላቂነት እና ወጥነት ያለው መሆን ነው። በተጨማሪ ትጋት ማለት ሥራ አለመፍታትና ተግባርን እስከ ፍፃሜው ይዞ መዝለቅ ነው።

 

ትጋት ሁልጊዜ 

  1.  ለዓላማ
  2.  ለግብ
  3. ለውጤት ይጨነቃል

ክርስቲያን፣ አገልጋይና ትጋት

በቤተ ክርስትያን አገልጋይ ሊጠነቀቅና ሊያስብበት ከሚገቡ ነገሮች አንዱና ዋነኛው ትጋቱ ነው፡፡ የማየተጋ አገልጋይ በምንም ተዓምር ፍሬያማና ውጤታማ መሆን አይችልም፡፡ ትጋት የጎደለው አገልጋይ ፍሬያማነቱ አይታይም ቀጣይነቱም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ይሆናል፡፡ አገልጋይ ሁልጊዜ በፍሬ መታየት አለበት፡፡ ውጤታማ ካልሆነ ግን ትጋቱ በጥያቄ ውስጥ የሚገባ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ እራሱ በትጋቱ ይታወቃል፡፡ በተለይ ለፀሎት ይተጋ ነበር፡፡ የማይተጋ አገልጋይ አገልግሎቱም እራሱም ከአገልግሎት ይቆማሉ፡፡ ወደ ደቀመዛሙርቱም መጣ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን፡- እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳን ልትተጉ አልቻላችሁምን ማቴዎስ 26፡40::

ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ ራሱ እየተጋ ክርስቲያን፤ አገልጋይ የማይተጋበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ስለዚህ ለክርስትናችንም ይሁን ለአገልግሎታችን ትጋት እጅግ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ስለዚህ ትጋት

1.  ትዕግስትን

2.  ጊዜን

3.  አላማን

4.  ግብን አተኩሮ ይንቀሳቀሳል፡፡

 

የትጋት ባህሪያት

1.  የጊዜ ብክንት የለበትም

2.  አይዘናጋም

3.  ሁልጊዜ በሥራ ላይ ነው

4.  ቸልተኝነት አይታይበትም

5.  ትኩረቱ ግቡ ላይ ነው

6.  ፅናት ይታይበታል

7.  ትዕግስት መለያ ባህሪው ነው

 

በትጋት ምን እናድርግ

1.  ስንገዛ በትጋት እንገዛ

ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምትገዙ በትጋትና በበጎ ፈቃድ ተገዙ ኤፌሶን 6፡7

2.  የምናደርገውን በትጋት እናድርግ

ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉ ቆላስይስ 3፡23

3.  እስከመጨረሻ መቆየት

…ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን እብራውያን 6፡11-12

4.  እናምልክ

…ሌሊትና ቀን በትጋት እያመለኩ ይደርስ ዘንደ አለኝታ አላቸው የሐዋሪያት ሥራ 26፡7

 

ትጋት ከየት ይመጣል

ትጋ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ነው፡፡

ነገር ግን በቲቶ ልብ ስለእናንተ ያንን ትጋት የሰጠ አምላክ ይመስገን፡፡ 2ኛ ቆሮንቶስ 8፡16

 

የትጋት ጥቅም

1.  ራስን/ ለፍስን ለመጠበቅ

ነፍስህን በትጋት ጠብቅ ዘዳግም 4፡9-10

2.  ሥራን ለመሥራት

ያም ሥራ በትጋት ይሠራል ዕዝራ 5፡8

 

ትጋት ለማን ነው

1. ለራስ ነው፡- የሚተጋ ሰው በስንፍና አይታማም፡፡ ምክንያቱም ስንፍና በራሱ ኃጢያት ነው፡፡ የማይተጋ ተቃራኒው ታካች ነው፡፡ ታካችን ስንፍና ይገድለዋል፡፡ እነሆ በባሪያዎቹ አይታመንም መለእክቱንም ስንፍና ይከሳቸዋል፡፡ ኢዮብ 4፡18 ስለዚህ ክስ ካለ ጥፋተኝነት ታይቷል ማለት ነው፡፡ ሰነፍን በሙቀጫ ውስጥ ከእህል ጋር በዘነዘና ብትወቅጠው ስንፍናው ከእርሱ አይርቅም፡፡ ምሳሌ 27፡22::የሞቱ ዝንቦች የተቀመመውን የዘይት ሽቱ ያገሙታል እንዲሁም ትንሽ ስንፍና ጥበብንና ክብርን ያጠፋል፡፡ መክብብ 10፡1::

2.  ለቤተክርስቲያን ነው፡- ቤተክርስቲያን አደገች ስንል ሥራዋን፣ተልዕኮዋን በትጋት እየፈፀመች መሆኑን መገመት ይቻላል፡፡ የምትተጋ ቤተክርስቲያን ዕድገቷ የሚታይ ነው፡፡ የማትተጋ ቤተ ክርስቲያን ባታድግም ባለበት መሄዷ አሊያም ከሌሎች ካደጉ ቤተክርስቲያናት አንፃር ስትታይ ዘገምተኛ ወይም ወደ ኋላ የቀረች ናት፡፡ ቤተክርስቲያን አደገች ካልን በፀጋ፣ በቃል ሙላት፣ በወንጌል ስርጭት፣ ቤተክርስቲያን ተከላ፣ የሰዎች መዳን ታየ ካልን በስሯ ያሉ አገልጋዮች በትጋት ስራቸውን እየከወኑ ነው፡፡ ስለዚህ ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፡፡2ኛ ጴጥሮስ 1፡5፡፡

 

3.  ለወንጌል ሥራ፡- እርግጥ ነው ጌታ ኢየሱስ በዋናነት የመጣው ለጠፉት፣ ከጌታም በኃጢያ ምክንያት የተለዩትን ለመፈለግና ለማዳን ስለሆነ ጌታ በሰጠን አደራ ልንተጋ ይገባልም የግድም ነው፡፡ ስለዚህ መትጋት የግድ ነው፡፡ እንዲህም አላቸው፤ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፤ ማርቆስ 16፡15፡፡ እነርሱም በዚሁ መሠረት ወጥተው ወንጌልን እየሰበኩ በየቦታው ሁሉ ሕመምተኞችን እየፈወሱ በየመንደሩ ያልፉ ነበር።ሉቃስ 9፡6፡፡እነርሱም በዚሁ መሠረት ወጥተው ወንጌልን እየሰበኩ በየቦታው ሁሉ ሕመምተኞችን እየፈወሱ በየመንደሩ ያልፉ ነበር።የሐዋሪያት ሥራ 8፡25::

 

ስለዚህ ትጋታችን በምን ላይ ይሁን?

መፅሃፍ ቅዱሰ ሲናገር ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ ለጌታ ተገዙ ሮሜ 12፡11

 

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ትጋት ብቻ ተናግሮ አያበቃም፤ ይልቁንም የምንተጋበትን ጉዳይና በምን መትጋት እንዳለብን ጭምር ይነግረናል። የእግዚአብሔር ቃል በብዙ ቦታ ትጉ ይላል። የምንተጋባቸውን ሲገልፅልን፡-

  1. በቃል እንትጋ፡- እኛ ግን ለፀሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን፡፡ የሐዋሪያት ሥራ 6፡4
  2. በህብረት እንትጋ፡- በሐዋሪያት ትምርና በኅብረት እንጀራውንም በመቁረስ በየፀሎቱም ይተጉ ነበር፡፡ የሐዋሪያት ሥራ 2፡42፡፡ እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማሪያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ የሐዋሪት ሥራ 1፡14::
  3. በሥራ፦ የታካች እጅ ችግረኛ ታደርጋለች፤ የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች። 5 በበጋ የሚያከማች ልጅ አስተዋይ ነው፤ በመከር የሚተኛ ግን እርሱ ራሱን ያስነውራል።  ምሳሌ 10፥4፡፡ የታካች ሰው ነፍስ ትመኛለች፤ አንዳችም አታገኝም፤ የትጉ ነፍስ ግን ትጠግባለች።ምሳሌ 13፥4
  4. በጸሎት፦ እኛ ግን ለፀሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን፡፡ የሐዋሪያት ሥራ 6፡4
  5. በአገልግሎት፦ “ጌታን ለማገልገል በመንፈስ የጋላችሁ ሁኑ እንጂ ከዚህ ትጋት ወደ ኋላ አትበሉ።” ሮሜ 12፥11፡፡
  6. በመልካም ሥራ፦ “ማንም ለሌላው በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፥ ነገር ግን ሁልጊዜ እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ።” 1ኛ ተሰ. 5፥15::

መትጋት ያለብን ለምንድነው?

መጽሐፍ ቅዱስ የትጋትን አስፈላጊነት በግልጽ እና በአንክሮ ይናገራል። የእግዚአብሔር ቃል መትጋት ያለብንን ሲያስተምረን፦

  1. ለክርስቶስ ምፅአት ለመዘጋጀት፡- "ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም። ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም።" ማር. 13፥32-36
  2. ወደፈተና እንዳንገባ ነው። “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉ ጸልዩም፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች፥ ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።” ማር. 14፥38
  3. ወደፊት ሊመጣ ካለው፣ከሚመጣው ሁሉ ለማምለጥና በሰው ልጅ ፊት ለመቆም ነው። “እንግዲህ ሊመጣ ካለው ከዚህ ሁሉ ለማምለጥ፥ በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትችሉ ስትጸልዩ ሁል ጊዜ ትጉ።” ሉቃ. 21፥36
  4. መጠራታችንንና መመረጣችንን ለማጽናት ነው። “ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና።” 2ኛ ጴጥ. 1፥10
  5.  ለመግዛት ነው። “የትጉ እጅ ትገዛለች፤ የታካች እጅ ግን ትገብራለች።” ምሳ. 12፥24
  6. ለባለጠግነት/ ባለጠጋ ለመሆን ነው። “የታካች እጅ ችግረኛ ታደርጋለች፤ የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች።” ምሳሌ 10፥4

የትጋት ጠላት ወይም ፀር

1.  መታከት

የታካች እጅ ጭግረኛ ታደርጋለጭ የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች ምስሌ 10፡4

2.  ስንፍና

ከስንፍናዬ የተነሳ ቁስሌ ሸተተ በሰበሰም መዝሙር 38፡5፡፡ የሰው ስንፍና መንገዱን ታጠምምበታለች ልቡም በእግዚአብሄር ላይ ይቆጣል፡፡ ምሳሌ 19፡3

3.  ሥራ ፈትነት

ተግባር መፍታት እንቅልፍን ታመጣበታለች የታካች ነፍስ ትራባለች፡፡ ምሳሌ 19፡15

4.  ዳተኝነት

በእምነትና በትዕግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እሰኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን፡፡ ዕብራውያን 6፡11-12፡፡

5.  ሥጋ

ወደ ፈተና እዳትገቡ ትጉና ፀልዩ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው፡፡ ማቴዎስ 26፡41

 

የሚተጉ ሰዎች ምልክት

1.  ስለ ጊዜ ጠንቅቀው ያውቃሉ

2.  ታጋሾች ናቸው

3.  ስንፍና አይታይባቸውም

4.  ለዓላማቸው ጨከኞች ናቸው

5.  የሚያዘናጉአቸውን አይሰሙም

6.  ከአላማቸው ጋር ከሚግባባና ከሚስማማ ጋር አብረው ይሠራሉ፣ ይዘልቃሉ

7.  ትኩረታቸው ሥራቸው ላይ ነው

8.  ትኩረታቸው ግብ ላይ ነው

9.  ለሚቃረኑዋቸው መልሰ አይሰጡም

 

የሚተጉ ሰዎች ከምንም በላይ ዋጋ የሚሰጡባቸው

1.  ለፀሎት ዋጋ ይሰጣሉ

2.  ለእግዚአብሔር ቃል ዋጋ ይሰጣሉ

3.  ለፀሎት ሰፊ ጊዜ ይሰጣሉ

በመጨረሻም

ስለዚህ ወንድሞች ሆይ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉም፡፡ 2ኛ ጴጥሮስ 1፡10::

 

ተባረኩ

አገልጋይ በረከት ሱላሞ ሱጌቦ

+25102910126/ +251911835440/ +251916276339

This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

---------------------------------------------------------------------

የእግዚአብሔር ሞገስ በሕዝቡ ላይ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

የእግዚአብሔር ሞገስ በሕዝቡ ላይ

የእግዚአብሔር ሞገስ

ሞገስ

ሞገስ ማለት ምን ማለት ነው? “ሞገስ” የሚለው ቃል “ካሪስ” ከሚለው ከግሪክ ቃል የተወሰደ እና የተዛመደ፣ አቻ ትርጉም ያለው ሲሆን የእግዚአብሔር ባለጠግነት ፣ ምህረት ፣ ነፃ ስጦታ ፣ ሽልማት ፣ ያልተገባ ወይም ለማይገባው፣ ሊገባውም ለማይችል ግን የተሰጠ፣ የተቸረ የሚልን ትርጉም ይይዛል፣ ይዟልም፡፡ 

 

ብዙውን እኛ ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር እንዲሰጠን ከምንፈልጋቸው ነገሮች አንዱ ሞገስ ነው። በእርግጥ እግዚአብሔር ቸር ነው፣ ለጋሽም ነው፣ ሰጪም ነው። ሆኖም ግን በመሠረታዊነት የምንስታቸው ወሳኝ ነገሮች፣ ከግንዛቤ የማናስገባቸው፣ ችላም የምንላቸው ናቸው። ግን እጅ ወሳኝ የሆኑ መሠረታዊ ነገሮች እና እውነታዎች ናቸው። እነዚህም መሠረታዊ ነገሮች ከእግዚአብሔር የምንፈልገውን ነገር የሚያሰጡን ናቸው። ቅድመ ሁኔታን አመላካች ናቸው። ስለዚህ አውቀን፣ ተረድተን ልናደርጋቸው፣ ልንተገብራቸው የግድ የሆኑ እና በቅድመ ሁኔታ ከእኛ የሚጠበቁ ናቸው። የሚጠበቅብንን ካደረግን በቀጣይ ከእግዚአብሔር የለመንነውንና የምንጠብቀውን ለመቀበል የምንችልበት ነው።

Read more: የእግዚአብሔር ሞገስ በሕዝቡ ላይ

የእግዚአብሔር ሞገስ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

             የእግዚአብሔር ሞገስ

ሞገስ

ሞገስ ማለት ምን ማለት ነው? “ሞገስ” የሚለው ቃል “ካሪስ” ከሚለው ከግሪክ ቃል የተወሰደ እና የተዛመደ፣ አቻ ትርጉም ያለው ሲሆን የእግዚአብሔር ባለጠግነት ፣ ምህረት ፣ ነፃ ስጦታ ፣ ሽልማት ፣ ያልተገባ ወይም ለማይገባው፣ ሊገባውም ለማይችል ግን የተሰጠ፣ የተቸረ የሚልን ትርጉም ይይዛል፣ ይዟልም፡፡ 

Read more: የእግዚአብሔር ሞገስ

ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋይ፤ አገልግሎትና አደራ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋይ፤ አገልግሎትና አደራ

ቤተ ክርስቲያን ባለቤቷ እግዚአብሔር እንደሆነ በሁሉም ዘንድ እሙንነት እና ተአማኒነት  ያለው ሐቅ ነው፡፡ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በምድር ላይ ሲተክል የራሱን አላማ፤እቅድና ግብ ኖሮት ሊያሳካ የመሰረታት ናት፡፡ ይህችም ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተዋጀች እና የተገዛች ነች፡፡

Read more: ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋይ፤ አገልግሎትና...

  • የይሁዳ መልዕክት
  • የተቃኘንበትን ቅኝት ያጠፉ ቅኝቶች
  • የታጠቀ ትውልድ
  • የትውልድ አደራ
  • እስክንድሮሶች

Article Categories

  • Literature/ስነ-ጽሑፍ
  • Gospel Thoughts / የወንጌል አስተምህሮ
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
  • Testimony/ምስክርነት
  • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን

Login Form

  • Forgot your password?
  • Forgot your username?
Copyright © 2026 yegizewkal. All Rights Reserved.