yegizewkal
ቃልህ ተገኝቶአል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ፥ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ። ትንቢተ ኤርምያስ 15፥16

  • Home/መነሻ ገጽ
  • Gospel Thoughts/የወንጌል አስተምህሮ
    • ነገረ ድነት/Salvation
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
    • Literature/ስነ-ጽሑፍ
    • ከመጽሐፍት ዓለም
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን
    • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Testimony/ምስክርነት
  • ማስታወቂያ/Advertisement
  1. You are here:  
  2. Home
  3. The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
  4. Literature/ስነ-ጽሑፍ

Literature/ስነ-ጽሑፍ

የታጠቀ ትውልድ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

የታጠቀ ትውልድ

 

በዘመናት ሁሉ በየትኛውም የአገዛዝ ስርአት አይነት ውስጥ መንግስታት፣ የመንግስታት መሪዎች ትልቁ ስጋታቸው እና ፍርሃታቸው የወጣቱ ትውልድ ቁጥር ነው። የቁጥራቸውና የብዛታቸው ማነስ ስጋትን ሲያጭር፣ የቁጥራቸው መብዛት የነገ ተስፋ ፍንትው ብሎ ይታያቸዋል። የቁጥራቸው መብዛት የነገ የደህንነት ስጋታቸውን በእጅጉ ይቀንሰዋል፣ ብቁና የጠነከረ ትውልድ መኖሩ ነገ ለሚመጣው አሉታዊ ነገር ምላሽ የሚሰጥበት አቅም እንዳለው ፍርሃትን ይቀንስለታል። 

ብዙውን ጊዜ ተፃራሪ መንግስታት አንዱ አንዱን መሠለል የዘወትር ሥራቸው ሲሆን ይህም ምን ያህል ለውትድርና ብቁ የሆነ ወጣት አለ? የመጠነ ሐብትስ ምን ያህል ነው? ተባብሎ መፈታተሹና አንዱ አንዱን መሠለሉ የአቅምን ሁኔታ ለማደርጀትና ለማጎልበት ግብዓት ይሆናቸዋል። 

Read more: የታጠቀ ትውልድ

ያልተጎሰመ አይን

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ


ያልተጎሰመ አይን

እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ እነዚህም ዝሙትና ርኩሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው፤ ቆላስይስ 3:5።

የሰው ልጅ ነገርን ከሚረዳበትና ከሚለይበት ነገሮች መካከል አንዱ አይን መሆኑ የማይካድ ሃቅ ነው። አበው በብሂላቸው እንኳኖ ሲያስቀምጡ "ነገር በአይን ይገባል" የሚሉት ብሂል  እውነታው የማያከራክርና የማያወላዳ ነው። አንዳንዴም ነገር እውነት ለመሆኑና ላለመሆኑ "አይኔን እያየህ አውራ" የሚሉትም እንዲሁ ነው። ነገር በአይን ይገባል፣ ይዘልቃልም። እንግዲህ ይህን ያህል ካልን እና ቢበቃ እንደው ያልተጎሰመ አይን ክፋቱን እና በህይወት በተለይ በእግዚአብሔር ዘንድ ባለን ምልልስ እና የክርስትና ህይወታችን ላይ የሚያመጣውን አሉታዊ ጣጣን እንመልከት። 

በተለይ ሥራ እያላቸው ሥራ ፈትተው የሚገኙ ሰዎች አይናቸው የማይፈለግን ነገር በማየት ተገቢ ያልሆነን ነገር በማድረግ ይታወቃሉ። ሥራ ያለው ሁልጊዜም ትኩረቱና እይታው ሥራ ላይ ብቻ ነው፣ በተለይ ለኃጢአት ጊዜና ቦታ ጨርሶውኑ የላቸውም። 

Read more: ያልተጎሰመ አይን

ጊዜ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

                          ጊዜ

መግቢያ

 ጊዜ እንደ ምንመገበው ምግብ፣ እንደምንጠጣው ውሃ እና እንደ  ምንተነፍሰው አየር ሁሉ ዋጋ  ያለውና በሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ትኩረት የሚያሻው ከእግዚአብሔር የተሠጠን ዕድል ነው። የሰው ልጅ በእያንዳንዱ የሕይወት እንቅስቃሴ እና ኑሮ  በሕይወት እስካለ ድረስ እድሜው ተወስኖ እና ተመጥኖ  የተሰጠው የጊዜ ልኬት ገደብ አለ። 

ላወቀ፣ ለተረዳና ለገባው ጊዜ ለሰው ልጅ ውዱ ሀብት ነው። ለሰው ልጅ ጊዜ ሲሰጥም ተመጥኖና ተወስኖ እንጂ እንደ አሸዋ የሚዘገን፣ ተዘግኖም የሚሰጥም የተሰጠም፣ የሚቸር የተቸረም አይደለም፣ ገደብ አለውና። አበው ሲናገሩ እንኳን "እድሜና ጤና ይስጠን እንጂ ብዙ እናያለን" የማንሠራውና የማናየው የለም የሚሉት በዚህ ምክንያት ነው። የጊዜን ብርታትና ጥንካሬንም ሲገልጹ "ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል"፤ ይህ ማለት ምን ያህል የጊዜን ሃያልነት እንደሚያውቁ መረዳት ሲቻል፣ በተጨማሪም ጉብዝናውን ለመግለፅ "ጊዜ ጎበዙ" በማለትም የውዳሴ ያህል በማሞካሸት ይገልጹታል። በእድሜ ዘመን የዕድሜ ልኬት ለሰው ልጅ የመኖሪያ ጣሪያው ለእያንዳንዱ ሰው የተሰጠው የጊዜ ገደብ ማለቂያ አለው። ልኬቱና መጠኑም የሚታወቀው ሲሰጥ ሳይሆን ሲያበቃና ሲያከትም ሲያልቅ ብቻ ነው። የጊዜ ዋጋንም የምናውቀው የዚያን ጊዜ ብቻ ነው። 

Read more: ጊዜ

ትጋት

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

 

------------------------------------------------------------------------------------------

 

 

ትጋት

“ለሰው የከበረ ሀብት ትጋት ነው”

(ምሳ. 12፥27)።

መግቢያ

በዚህ ዓለም ላይ ፍሬያማ ሠራተኛ ወይም ውጤታም ሠራተኛ የምንለው ሰው ለውጤታማነትና ለፍሬያማ ሠራተኝነት ከሚያበቃው ዋነኛ ነገር አንዱ ትጋት እንደሆነ የማይካድ ሐቅ ነው፡፡ የሚተጉ ሰዎች ዋነኛ መገለጫ ባህሪያቸው ለጊዜ ያላቸው የጠለቀ አመለካከት እና ዋጋ ትጋታቸውን ጨምሮላቸው ውጤታማ መሆነቸው ነው፡፡

የሚተጉ ሰዎች ሌላኛው ባህሪያቸው እጅግ ትዕግሰተኛ መሆናቸውና ሁልጊዜ ላለሙት ግብና ስኬት ዘወትር በትዕግስት እና እጅግ ብልሃት በታከለበት መንገድ ሥራን መከወናቸው ሲሆን ጥረታቸውን ለቅፅበት ያህል አለማቋረጣቸው ለትጋታቸው ግብዓት ሆኖ ተጠቅመው ግባቸው ላይ ይደርሳሉ፡፡

ትጋት ብዙ ጥረትን፤ የጊዜ አጠቃቀምነ፤ ትዕግስተኝነትን፤ መቋቋምን፤ ግብን ዓላማን ውጤትን ትኩረት አድርጎ የሚነሳ የሥራ መከወኛ ኃይል እና ብርታት ነው፡፡ ትጋት የጊዜን አጠቃቀም፤ ለጊዜ ዋጋን የሚሰጥ፤ ጊዜ እንዲባክን የማይፈልግ፤ ከሁሉ በላይ ለስንፍና ቦታ የሌለው አንዳች ኃይል ነው፡፡

ትዕግስት ከሌለ ትጋት የለም፤ ትጋት ከሌለ ስኬት የለም፤ ስኬት ከሌለ ቀጣይ ምዕራፍ አይታሰብም፡፡ ስለዚህ ትዕግስትና ትጋት በእጅጉ ተሰናስለው የሚኖሩ ነገሮች ናቸው፡፡

Read more: ትጋት

የእግዚአብሔር ሞገስ በሕዝቡ ላይ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

የእግዚአብሔር ሞገስ በሕዝቡ ላይ

የእግዚአብሔር ሞገስ

ሞገስ

ሞገስ ማለት ምን ማለት ነው? “ሞገስ” የሚለው ቃል “ካሪስ” ከሚለው ከግሪክ ቃል የተወሰደ እና የተዛመደ፣ አቻ ትርጉም ያለው ሲሆን የእግዚአብሔር ባለጠግነት ፣ ምህረት ፣ ነፃ ስጦታ ፣ ሽልማት ፣ ያልተገባ ወይም ለማይገባው፣ ሊገባውም ለማይችል ግን የተሰጠ፣ የተቸረ የሚልን ትርጉም ይይዛል፣ ይዟልም፡፡ 

 

ብዙውን እኛ ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር እንዲሰጠን ከምንፈልጋቸው ነገሮች አንዱ ሞገስ ነው። በእርግጥ እግዚአብሔር ቸር ነው፣ ለጋሽም ነው፣ ሰጪም ነው። ሆኖም ግን በመሠረታዊነት የምንስታቸው ወሳኝ ነገሮች፣ ከግንዛቤ የማናስገባቸው፣ ችላም የምንላቸው ናቸው። ግን እጅ ወሳኝ የሆኑ መሠረታዊ ነገሮች እና እውነታዎች ናቸው። እነዚህም መሠረታዊ ነገሮች ከእግዚአብሔር የምንፈልገውን ነገር የሚያሰጡን ናቸው። ቅድመ ሁኔታን አመላካች ናቸው። ስለዚህ አውቀን፣ ተረድተን ልናደርጋቸው፣ ልንተገብራቸው የግድ የሆኑ እና በቅድመ ሁኔታ ከእኛ የሚጠበቁ ናቸው። የሚጠበቅብንን ካደረግን በቀጣይ ከእግዚአብሔር የለመንነውንና የምንጠብቀውን ለመቀበል የምንችልበት ነው።

Read more: የእግዚአብሔር ሞገስ በሕዝቡ ላይ

የእግዚአብሔር ሞገስ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

             የእግዚአብሔር ሞገስ

ሞገስ

ሞገስ ማለት ምን ማለት ነው? “ሞገስ” የሚለው ቃል “ካሪስ” ከሚለው ከግሪክ ቃል የተወሰደ እና የተዛመደ፣ አቻ ትርጉም ያለው ሲሆን የእግዚአብሔር ባለጠግነት ፣ ምህረት ፣ ነፃ ስጦታ ፣ ሽልማት ፣ ያልተገባ ወይም ለማይገባው፣ ሊገባውም ለማይችል ግን የተሰጠ፣ የተቸረ የሚልን ትርጉም ይይዛል፣ ይዟልም፡፡ 

Read more: የእግዚአብሔር ሞገስ

ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋይ፤ አገልግሎትና አደራ

Details
Written by: Bereket Sulamo
Category: Literature/ስነ-ጽሑፍ

ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋይ፤ አገልግሎትና አደራ

ቤተ ክርስቲያን ባለቤቷ እግዚአብሔር እንደሆነ በሁሉም ዘንድ እሙንነት እና ተአማኒነት  ያለው ሐቅ ነው፡፡ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በምድር ላይ ሲተክል የራሱን አላማ፤እቅድና ግብ ኖሮት ሊያሳካ የመሰረታት ናት፡፡ ይህችም ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተዋጀች እና የተገዛች ነች፡፡

Read more: ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋይ፤ አገልግሎትና...

  • EECFNA
  • በመከራ ውስጥ የሚፀና ማንነት
  • በሚበልጥ ክብር መገለጥ
  • አልባሾችህን ጠንቅቀህ እወቅ
  • የይሁዳ መልዕክት

Article Categories

  • Literature/ስነ-ጽሑፍ
  • Gospel Thoughts / የወንጌል አስተምህሮ
  • The Feast of the Word/ከቃሉ ማዕድ
  • Testimony/ምስክርነት
  • Religious News/ሐይማኖታዊ ዜና
  • Churches/ቤተ ክርስቲያን
Copyright © 2026 yegizewkal. All Rights Reserved.