Home
ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም
- Details
- Category: ከቃሉ
ወደ ገላትያ ሰዎች 4፥7 "ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።"
"ልጅ ነህ!" ይህ የአዲስ ኪዳን የክርስቶስ ሥራና ትልቁ አዋጅ ነው።
እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ሥራ፣ ሞትና ትንሣኤው አማካኝነት ልጁ አድርጎናል። በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ይህም እምነት የእግዚአብሔር ፈቃድና የእግዚአብሔር ሥራ ነው። ዮሐንስ ወንጌል 6፡28-29። እንግዲህ በክርስቶስ በማመን ልጆች ከሆንን ምንም ነገር ተመልሶ ወደ ባርነት ሊወስደን አይችልም። ስለዚህ ደስ ይበለን፥ እኛ ከእግዚአብሔር የተወለድን ልጆቹ ነን እንጂ ባሪያዎች አይደለንም።
ልጅ ከሆንን እንግዲህ የእግዚአብሔር ወራሾ ነን። እግዚአብሔር የሰጠውን የሕይወት እና የመለኮት ባህርይ ተካፋይ እና ወራሾች ነን።
ስለዚህ ይህን ኢየሱስን ለመተዋወቅ ይህንን ጸሎት ይጸልዩ "ጌታ ኢየሱስ ሆይ፣ አንተ ስለ እኔ ተሰቅለሃል፣ ሞተሃል፣ ደግሞም ከሙታን ተነስተሃል። ይህንንም በልቤ አምናለሁ፣ በአፌም እመሰክራለሁ። አንተ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆንህ፣ ደግሞም ጌታ እንደሆንህ አምናለሁ እመሰክራለሁም። አሜን"
ይህ ጸሎት የእግዚአብሔር ልጅ አድርጎዎታል። እንኳን ወደዚህ ልጅነት እና ሕይወት ተሻገሩ።
የምትሰማው ድምጽ
- Details
- Category: ከቃሉ
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 17
አሰላለፍሀን ቀይር፣
ፍልስጤም እንደ ተሰለፈ አትሰለፍ፣ ፍልስጤም እንደ ተከማቸ አትከማች፤
አምላክህ እግዚአብሔር የሚለካ አምላክ ስላልሆነ ... አምላክህን በእምነትህ አትወስነው፤
የጌታ ደስታ
- Details
- Category: ከቃሉ
ዳይመንሽን
እንደ ቤተ ክርስቲያን ወይም እንደ ግለሰብ አዳዲስ ዳይሜንሽኖች በታናናሽ ምልክቶች ይጀምራሉ።
አዲስ ምልክት ካየህ አዲስ ዳይሜንሽን እየተጀመረ ነው ማለት ነው።
እግዚአብሔር ሙሴን በምድረ በዳ ውስጥ እያለ የህዝብ መሪ የሚሆንበትን ስበትና ልምምድ የጀመረው በታናሽ ምልክት ነው። የማያቃጥል እሳት አሳየውና ሳበው። ዘጸ. 3፤1-3
ታናሹን ምልክት ታላቅ ያደረገው ላኪው ነው። ከእግዚአብሔር ይሁን እንጂ ታናሹ ምልክት ታላቅ ነገር ከጀርባው አለው። ወደ አዲስ ዳይሜንሽን መግባት ትፈልጋለህ? ታናናሾቹን ምልክቶች እንደ እግዚአብሔር ቃል ተከተላቸው።
እግዚአብሔር ከስምህ በላይ ነው
- Details
- Category: ከቃሉ
ከስምህ እና ከተጠራህበት አቅም በላይ እግዚአብሔር እንድትኖር ይፈልጋል። ይህም ደግሞ የሚሆነው እግዚአብሔር በክርስቶስ የሰራልንን ስራ በማመን ብቻ ነው።
Page 1 of 4